Garage and vehicle maintenance
የኦሮሚያ መሬት ቢሮ የመስሪያ ቤቱ ተሽከርካሪዎችን ከህጋዊ ጋራዥ አወዳድሮ ማስጠገን ይፈልጋል
Description
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የኦሮሚያ መሬት ቢሮ የመስሪያ ቤቱ ተሽከርካሪዎችን ከህጋዊ ጋራዥ አወዳድሮ ማስጠገን ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ጋራዦችን በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል::
- ተወዳዳሪዎች የዘመኑን ግብር የከፈሉና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ እና ውል ገብቶ በተባለው ጊዜ ውስጥ ተሽከርካሪዎችን ጠግኖ በጊዜ ጨርሶ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር TIN NO ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 100/አንድ መቶ/ በመክፈል በኦሮሚያ መሬት ቢሮ 3ኛ ፎቅ ፋይናንስ ክፍል መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ CPO ለመወዳደር ዋጋ 150,000.00 (አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጥገናውን የዋጋ ዝርዝር በጨረታ ማወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ስማቸውን፣ፊርማቸውንና አድራሻቸውን በማስፈርና ማህተም በማድረግ የጨረታ ዶክመንት ፋይናንሻል ኦርጅናል እና ኮፒውን ቴክኒካል ኦርጅናል እና ኮፒውን እንዲሁም CPO በተለያየ (በአምስት ፖስታ) በታሸገ ኤንቨሎፕ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወይም ባይገኙም ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም ከቀኑ በ7፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ8፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
- የጨረታ ሣጥኑ ከታሸገ ወይም ከተከፈተ በኋላ የሚቀርብ ማንኛውም የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለተጨማሪ መረጃ በዚህ ስልክ ቁጥር መጠቀም ይችላሉ። 0946653304/094944572/09106 22700/0919519951
አድራሻ ፡- ሳርቤት አደባባይን ዞሮ ወደ ቄራ መሄጃ ዋናው አስፋልት 200 ሜትር ላይ
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት መስሪያ ቤቶች ቅጥር ግቢ ውስጥ
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት
መስተዳደር የኦሮሚያ መሬት ቢሮ
Tender details
- Deadline: 2026-08-31
- Bid closing time: 13:00
- Bid opening: 2026-08-31 14:30
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Oromia Land Bureau
- Buyer address: ሳርቤት አደባባይን ዞሮ ወደ ቄራ መሄጃ ከዋናው አስፋልት 200 ሜትር የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት መስሪያ ቤቶች ቅጥር ግቢ ውስጥ
- Bid bond: 150,000.00 ብር
- Bid document price: 100.00 ብር
- Published on: Addis Zemen (Aug 08, 2026)
- Posted at: 2026-08-08T08:04:56.000Z