Office furniture
በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት የተለያዩ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
Description
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 01/2019
በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት በወረዳው ላሉ ጽ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል 1ኛ ዙር ጥቅል ግዥ ማለትም
1.የጽሕፈት መሣሪያ፣2.የደንብ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ 3. አላቂ የጽዳት ዕቃወች 4.የኤሌክትሮኒክሰ 5.የመኪና ጎማዎች 6.ህትመት 7.መስተንግዶ ውሃና ቆሎ/ 8.የደንብ ልብስ ስፌት 9.የሃገር መኪና ኪራይ 10.ዲኮርና ድንኳን ኪራይ፡11.የኤሌክትሮኒክስ ጥገና እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ህጋዊ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል።
1. በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ ከገቢዎች ከሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ እና በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ ሆነው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
2. ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆነ እና የምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
3. የጨረታ ሰነዱን ለአንዱ ሎት የማይመለስ 300(ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ይህን ጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ከጠዋት 2፡30 – 6፡30 ከሰዓት 7፡30-11፡30 ሰዓት በወረዳው ፋይናንስ ጽ/ቤት አዲሱ ህንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 203 መግዛት ትችላላችሁ።
4. ተጫራች ከዚህ በታች የተጠቀሰዉን የጨረታ ማሰከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ መቅርብ አለባቸዉ
|
ሎት ቁጥር |
የሎት ዝርዝር |
የጨረታ ሰነድን የማይመለስ ብር |
የተጠቀሰዉ የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ በኢትዮጵያ ብር |
|
ሎት1 |
አላቂ የጽፈት መሳሪዎች |
300 |
27,600 |
|
ሎት2 |
የደንብ ልብስ |
300 |
56,700 |
|
ሎት3 |
ኣላቂ የጽዳት ዕቃዎች |
300 |
45,900 |
|
ሎት4 |
የኤሌትሮኒክስ እቃዎች |
300 |
20,600 |
|
ሎት5 |
የመኪና ጎማዎች |
300 |
10,000 |
|
ሎት6 |
ህትመት |
300 |
12,400 |
|
ሎት7 |
መስተንግዶ |
300 |
6000 |
|
ሎት8 |
የደንብ ልብስ ስፌት |
300 |
3000 |
|
ሎት9 |
የሃገር መኪና ኪራይ |
300 |
6000 |
|
ሎት10 |
ዲኮር ድንኳን እና ጀነሬተር ኪራይ |
300 |
5000 |
|
ሎት11 |
የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች |
300 |
5600 |
5. የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሰከረለት ሲፒኦ ለእያንዳንዱ ሎቶች ለየብቻ ከላይ በሰንጠረዡ በተገለጸው መሰረት በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት ስም ማስያዝ አለባቸው።ከሲፒኦ ውጭ ምንም አማራጭ የማንቀበል መሆኑን እንገልጻለን።
6. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን መሥሪያ ቤቱ በሰጣቸው የአንዱ ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስ እና ጠቅላላ ዋጋ በሚለው ቦታ ላይ ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው በመሙላትና የድርጅታቸውን ማህተም ፊርማና ሙሉ ስም አድራሻቸውን በመግለጽ፤ የቴክኒካልና የፋይናንሽያል ኦርጂናል በአንድ ፖስታ ላይ ኮፒያቸውን ለብቻ በሌላ ፖስታ በማሸግ ባጠቃላይ ለአንድ ሎት ሁለት ፖስታ ብቻ ላይ በማሸግ ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት በፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 203 ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።ሁሉንም ሎቶች ለየብቻ አሽገው የማያቀርቡ ተወዳዳሪዎች ከውድድሩ ውጪ ይደረጋሉ።
7. ተጫራቾች የሚያቀርቧቸውን ዕቃዎች ዓይነት ለመለየት የሚያስችል ናሙና ለተጠየቀባቸው እቃዎች ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ አለባቸው ናሙና ከላቀረቡ ጨረታ መሳተፍ አይችልም ።
8. የጨረታ ሳጥኑ በ11ኛው ቀን ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ይታሸጋል በዚሁ ቀን 4፡30 ጨረታው ተጫራቾች | ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። በመሆኑም ከተጠቀሱት ቀንና ሰዓት ውጪ የሚቀርቡ ማንኛውም የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት አይኖራቸውም።
9. የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት 11 ኛው ቀን በዓል ከሆነ የሚቀጥለው የስራ ቀን 4፡ 00 ሰዓት ይታሸጋል በዚሁ ቀን 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
10. ለጨረታው የሚቀርቡ ዕቃዎች ጥራታቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ መሆን አለባቸው፡፡ያሸነፉበትን ዕቃ በራሳቸው ወጪ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07 ፋ/ጽ/ቤት ግምጃ ቤት ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል።
11. ተጫራቾች የጨረታው አሸናፊ ሆነው ከተገኙባቸው ዕቃዎች ከአጠቃላይ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በማስያዝ ከጽ/ቤት ጋር የግዥ ውል ስምምነት በመፈራረም ከተፈረመበት ቀን አንስቶ ባሉት ተከታታይ 7(ሰባት) የሥራ ቀናት ዕቃዎችን ማስረከብ ይኖርባቸዋል።
12. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኝ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ እና 20 % ጨምሮ ወይም ቀንሶ የመግዛት መብቱ የተጠበቀ ነው።
13. ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በአካል በመቅረብ ከመገናኛ ወደ ሰዓሊተ ምህረት ቤ/ክ በሚወስደው መንገድ ጉርድ ሾላ በሻሌ ሆቴል ፊት ለፊት ወይም በስልክ ቁጥር 011-812-24-86 ደዉለዉ መጠየቅ ይችላሉ።
በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ፋይናንስ ጽ/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-08-21
- Bid closing time: 12:00
- Bid closing (note): ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት
- Bid opening: 2026-08-21 12:00
- Bid opening (note): ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን 4፡30 ሰዓት
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Bole Sub City Woreda 7 Administration Finance and Economic Development Office
- Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
- Bid document price: በየሎቱ 300.00 (ሶስት መቶ ብር)
- Published on: Addis Zemen (Aug 09, 2026)
- Posted at: 2026-08-10T07:39:37.000Z