Stationery

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወረዳ 03 ፋይናንስ ፅ/ቤት የተለያዩ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ 1ኛ ዙር ቁጥር 001

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወረዳ 03 ፋይናንስ ፅ/ቤት ከዚህ በታች በሎት የተደራጁ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

  • ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ እቃዎች እና ሌሎች
  • ሎት 2  ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች
  • ሎት 3 የደንብ ልብሶች
  • ሎት 4. የጽዳት እቃዎች ስፖርት መገልገያ እቃዎች የመኪና እና የሞተር ሳይክል ጎማ
  • ሎት 5. መድሃኒት እና የተለያዩ ዘሮች
  • ሎት 6. የቋሚ እቃዎች
  • ሎት7. ህትመትና ሌሎች
  • ሎት 8. የትራንስፖርትና ጭነት አገልግሎት

በመሆኑም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 200(ሁለት መቶ ብር) በመክፈል በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር ፋይናንስ ፅ/ቤት ካራ ቆሬ የሚገኘው ህንፃ ቀርበው መውሰድ እንደሚችሉ እናሳውቃለን።

ተጫራቾች ማሟላት የሚኖርባቸው።

  • የዘመኑን የታደሰ የንግድ ፈቃድና የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው።
  • የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የአስገቡት ዋጋ ለሁሉም ሎት 1.5 % በሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው።
  • ተጫራቾች በጥቃቅንና አነስተኛ ከተደራጁ ሲፒኦ ማስያዝ አይጠበቅባቸውም በምትኩ የዋስትና ደብዳቤ ማቅረብ አለባቸው። የሚቀርበው ደብዳቤ በኃላፊ መፈረም አለበት።
  • የቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው የሚቀርበው የዋጋ ሰነድ ለቫት ተጠቃሚዎች ቫትን ያካተተ መሆን አለበት።
  • ትራንስፖርት ላይ ለሚወዳደሩት የተሽከርካሪ ባለቤትነት መታወቂያ ወይም ሊብሬ ኮፒ ማቅረብ ይኖርበታል።
  • ከትራንስፖርት ውጪ ማንኛውም ተጫራች የታሸገ ፖስታ ላይ የድርጅቱ ማህተም መኖር አለበት።
  • ማንኛውም ተጫራች የሚያቀርበው ሰነድ ኮፒና ዋና ማቅረብ ይኖርበታል።
  • ለሎት 8 ብቻ ማሟላት የሚገባውን ሰነድ ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ ከሆኑ የሚበረታታ ሲሆን ይህን ማቅረብ ካልተቻለ በምትኩ ቲኦቲ ወይም 2% ከፋይ መሆን ይኖርበታል።
  • አሸናፊ ተጫራች በሰነድ ውስጥ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ቀርቦ ውል መዋዋል አለባቸው።
  • የእቃ ማስረከቢያ ቦታ ወረዳ 03 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት ይሆናል።
  • ተጫራቾች ለሚያቀርቡት እቃ ናሙና ማቅረብ አለባቸው። ናሙና ያላቀረበ ድርጅት ከውድድር ውጪ ይሆናል። እቃው በናሙናው ላይ ያለውን የጥራት ደረጃ ይዞ ካልተገኘ ተመላሽ ይደረጋል።
  • ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ከላይ የተጠቀሱትን መረጃዎች በማቅረብ ለጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ መውሰድ ይችላሉ።
  • ተጫራቾች ተወዳድረው ያሸነፉባቸውን እቃዎች በወቅቱ ማቅረብ ካልቻሉ ያስያዙት ሲፒኦ ይወረሳል።
  • አሸናፊ ድርጅት ያሸነፉበትን እቃ 10% ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  • አሸናፊ ድርጅት ውል ከገባበት ቀን ጀምሮ በ10 (አስር ) ቀን ውስጥ እቃውን ማቅረብ ይኖርበታል።
  • አንድ ተጫራች በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት አይችልም።
  • የጨረታው ሳጥን ጨረታው አየር ላይ ከዋለ ከ10 የስራ ቀን በኋላ በአስራ አንደኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በወረዳው አስተዳደር ፋይናንስ ፅ/ቤት ውስጥ ይከፈታል።
  • ተጫራቾች ተወዳድረው ያሸነፉባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ቦታው ድረስ ማቅረብ አለባቸው።
  • ተጫራቾች (በጨረታው) የተሸነፉ ድርጅቶች የጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ሲፒኦ ተመላሽ ይሆናል። ጽ/ቤቱ ሌላ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ
መስሪያ ቤቱ የሚገኝበት ልዩ ቦታ ካራ ቆሬ ሩታ ከግራር 200 ሜትር ገባ ብሎ ወረዳ 03 ፋይናንስ ጽ/ቤት መሆኑን እንገልጻለን።
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወረዳ 03 ፋይናንስ ፅ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-08-21
  • Bid closing time: 10:00
  • Bid closing (note): የጨረታው ሳጥን ጨረታው አየር ላይ ከዋለ ከ10 የስራ ቀን በኋላ በአስራ አንደኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-08-21 10:30
  • Bid opening (note): የጨረታው ሳጥን ጨረታው አየር ላይ ከዋለ ከ10 የስራ ቀን በኋላ በአስራ አንደኛው ቀን በ4፡30 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Kolefe Keranio Sub City Administration Woreda 03 Finance Office
  • Bid bond: ለሁሉም ሎት 1.5 %
  • Bid document price: ለእያንዳንዱ ሎት 200(ሁለት መቶ ብር)
  • Published on: Addis Zemen (Aug 10, 2026)
  • Posted at: 2026-08-11T07:43:21.000Z
← Back to all tenders