Stationery

የኢሉ ወረዳ ፍርድ ቤት ለመስሪያ ቤቱ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎችን፤ የደንብ ልብስ፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን፣ የመኪና ጎማ፣ ቋሚ የቢሮ ዕቃዎችን፣ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ

ቁጥር 01/2018

የኢሉ ወረዳ ፍርድ ቤት ለመስሪያ ቤቱ

  • የጽህፈት መሳሪያዎች፣
  • የጽዳት ዕቃዎችን፤
  • የደንብ ልብስ፣
  • የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን፣
  •  የመኪና ጎማ፣
  • ቋሚ የቢሮ ዕቃዎችን፣ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት

 ስለሚፈልግ በጨረታው ላይ ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች ሁሉ፡-

  1. የዘመኑን የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2.  ተጫራቾች የዕቃዎቹን ዝርዝር ሰነድ የማይመለስ ብር 400 በመከፈል ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ 10 ተከታተይ የሥራ ቀናት በደቡብ ምዕ/ሸዋ ዞን በኢሉ ወረዳ ፍ/ቤት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 4 እየቀረቡ መግዛት ይችላሉ፡፡
  3.  ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ ቢድ ቦንድ ብር 5000 /አምስት ሺህ/ በባንክ በተመሰከረላት ሲ.ፕ.ኦ ፤ቼክ ወይም ጥሬ ገንዛብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  4.  ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ በሰም በተሸገ እንቭሎፕ ከላይ በተራ ቁጥር 2 በተጠቀሰው አድራሻ ለዚህ ለተዘጋጀው ሳጥን በ 11ኛው ቀን ከ ጠዋቱ 3፡00 እስከ ቀኑ 6፡00 ድረስ ማስገበት ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ጨረታው በ11ኛ ቀን ከቀኑ በ 8፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ህጋዊ ወክሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተራ ቁጥር 2 በተገለጸው ቦታ ይከፈታል፡፡
  6.  በተራ ቁጥር 4 እና 5 ላይ የተገለፀው ከኛው ቀን ዕለቱ የበዓል ቀን ላይ ከዋለ ወይም ዕለቱ ዝግ ከሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሣሳይ ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡
  7.  አሸናፊው አሸነፊነቱ ከታወቀበት ቀን ጀምሮ እስከ 10 ባሉ ቀናቶች በኢሉ ወረዳ ፍርድ ቤት ታጂ ከተማ ከአ/አ 55 ኪ/ሜትር ላይ በራሱ መጓጓዠ ዕቃዎቹን አቅርቦ ማስረከብ ይኖረበታል፡፡
  8. ተጫራቾች በጨረታው መሠረት ዕዋዎቹን ሙሉ ከአስረከቡ ክፍያው ወዲያውኑ ይፈፀማል፡፡
  9. መ/ቤቱ የተሻለ አማረጭ ካገኘ ጨርታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ተጨማሪ ማብራርያ ከፈለጉ ስልክ ቁጥር 0113390051/0938620309

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን የኢሉ ወረዳ ፍ/ ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-09-04
  • Bid closing time: 12:00
  • Bid closing (note): ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ 11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 እስከ ቀኑ 6፡00
  • Bid opening: 2026-09-04 14:00
  • Bid opening (note): ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛ ቀን ከቀኑ በ 8፡00 ሰዓት
  • Region: Oromia
  • Publishing entity: Ilu Woreda Court
  • Bid bond: 5000.00 ብር
  • Bid document price: 400.00 ብር
  • Published on: Addis Zemen (Aug 24, 2026)
  • Posted at: 2026-08-26T07:37:58.000Z
← Back to all tenders