Cleaning and Janitorial Equipment and Service

በየካ/ክ/ከ ወረዳ 02 አስተዳደር የፋ/ጽ/ቤት ለ2019 በጀት አመት አላቂ የቢሮ ዕቃ (እስቴሽነሪ)፣ ቋሚ ዕቃ (የአዳራሽ/ኮንፈረንስ ወንበር፣ የደንብ ልብስ፣ የፅዳት ዕቃ፣ የትራንስፖርት አገልግሎት፣ ህትመት አገልግሎት፣ የዲኮር ስራ፣ ሞንታርቦ፣ ጄኔሬተር እና ወንበር ኪራይ አገልግሎት፣ የጥገና (የአይቲ) ስራ አገልግሎት፣ የመስተንግዶ አገልግሎት፣ የሰራተኞች ካፌ አገልግሎት፣ የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎች

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

በየካ/ክ/ከ ወረዳ 02 አስተዳደር የፋ/ጽ/ቤት ለ2019 በጀት አመት አላቂ የቢሮ ዕቃ (እስቴሽነሪ)፣ ቋሚ ዕቃ (የአዳራሽ/ኮንፈረንስ ወንበር፣ የደንብልብስ፣ የፅዳት ዕቃ፣ የትራንስፖርት አገልግሎት፣ ህትመት አገልግሎት፣ የዲኮር ስራ፣ ሞንታርቦ፣ ጄኔሬተር እና ወንበር ኪራይ አገልግሎት፣ የጥገና (የአይቲ) ስራ አገልግሎት፣ የመስተንግዶ አገልግሎት፣ የሰራተኞች ካፌ አገልግሎት፣ የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎች እና ጌጣጌጥ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት የምትችሉ ነጋዴዎች መወዳደር ትችላላችሁ።

  • የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ።
  • የእሴት ታከስ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልፅ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ።
  • በሚሰጠው አገልግሎት ከመ/ቤቱ ጋር ውል ወስዶ በሚፈለገው ሰዓት ማቅረብ እና አገልግሎቱን መስጠት የሚችል።
  • በአቅራቢነት ዝርዝር የተመዘገቡ መሆናቸውን ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ።
  • ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት የካ ከፍለ ከተማ ወረዳ 2 ፋ/ጽ/ቤት የጨረታ መመሪያ፣ የዕቃና አገልግሎት ስፔስፍኬሽን አጠቃሎ የያዘ የጨረታ ሰነድ በአካል መጥተው ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ) ብቻ ገዝተው መውሰድ ይችላሉ።
  • አሸናፊ በሚሆኑበትን ዕቃ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በጥሬ ማስያዝ የሚችል።
  • ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሲሆን በ11ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ 4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት የሚከፈት ሲሆን የሚከፈትበት ቀን እሁድ እና ቅዳሜ /የበዓል/ ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል።
  • የጨረታ ማስከበሪያ በተመለከተ የደንብ ልብስ 13,000 (አስራ ሶስት ሺህ)፣ እስቴሽነሪ 5,000.00 (አምስት ሺህ)፣ የፅዳት ዕቃ 5,000.00(አምስት ሺህ)፣ ትራንስፖርት 5,000(አምስት ሺህ)፣ ህትመት 5,000.00(አምስት ሺህ)፣ ጥገና አገልግሎት 3,000.00(ሶስት ሺህ)፣ የመኪና መለዋወጫ 5,000.00(አምስት ሺህ)፣ የሰራተኞች ካፌ አገልግሎት 5,000.00 (አምስት ሺህ) እና የቢሮ መስተንግዶ አገልግሎት 3,000.00 (ሶስት ሺህ) CPO ብቻ ማስያዝ እንዳለባቸው እየገለፅን በድጋፍ ደብዳቤ ለምታመጡ ነጋዴዎች የምታስገቡት ዕቃ በሀገር ውስጥ ለሚመረቱ ዕቃዎች፣ ለትራንስፖርት፣ ለህትመትና ለጥገና እና ለመስተንግዶ አገልግሎት የምናስተናግድ ሲሆን ከሀገር ውጪ ለሚመረቱ/ለሚገቡ ምርቶች በድጋፍ ደብዳቤ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን።
  • ለሚያቀርቡት ዕቃ ናሙና ጨረታ ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ ግዴታ ነው።
  • መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ፡- ፈረንሳይ ለጋሲዎን ማዞሪያ አደባባይ 100 ሜትር ገባ ብሎ የካ ክ/ከ ወረዳ 02 አስተዳደር አንደኛ ፎቅ ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 9

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 011 154 8903 መደወል ይችላሉ

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-09-09
  • Bid closing time: 10:00
  • Bid closing (note): ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሲሆን በ11ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-09-09 10:00
  • Bid opening (note): ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሲሆን በ11ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Yeka Sub City Woreda 2 FEDB
  • Buyer address: ፈረንሳይ አደባባይ ፊት ለፊት 100 ሜትር ገባ ብሎ
  • Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
  • Bid document price: 300.00 ብር ለእያንዳንዱ ሎት
  • Published on: Addis Zemen (Aug 28, 2026)
  • Posted at: 2026-08-28T09:37:10.000Z
← Back to all tenders