Building Construction

የአርባ ምንጭ ከተማ ፋይናንስ ፕላን ልማት መምሪያ አንድ ብሎክ ባለ አምስት ክፍል እና አንድ ብሎክ ባለ ሦስት ክፍል ግንባታ በደረጃ 8 እና ከዚያ በላይ በተደራጁ ማህበራት አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

የአርባ ምንጭ ከተማ ፋይናንስ ፕላን ልማት መምሪያ ለአ/ም/ከ ትምህርት መምሪያ ገሮ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ለምገነባው ሳይት፡-

  • LOT-1 አንድ ብሎክ ባለ አምስት ክፍል እና
  • LOT-2 አንድ ብሎክ ባለ ሦስት ክፍል ግንባታ በደረጃ 8 እና ከዚያ በላይ

በተደራጁ ማህበራት አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡

ስለዚህ መስፈርቱን የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንድትወዳደሩ ተጋብዛችኋል፡፡

  1.  በዘርፍ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው
  2. የግብር ከፋይ ቁጥር (TN No) ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ
  3. አቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማስረጃ ኦላይን online/ ማቅረብ የሚችል።
  4.  በግንባታውን ዘርፍ መልካም የሥራ አፈፃፀም ያለው/ላት ሆነው ከዚህ በፊት በወሰዱት ስራ ከ95% በላይ አፈጻጸም ያለው እና ስራ በከተማው አስተዳደሩ የተሰጠ ከሌለም ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ስራ ሰርቶ ምንም ዓይነት ቅሬታ ያልቀረበበት መሁኑን ማረጋገጫ ከማዘጋጃ ቤት ኮንስትራክሽን ዘርፍ ማቅረብ የሚችል ፡፡
  5.  ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ለእያንዳንዱ ጨረታ 70,000.00 /ሰባ ሺህ ብር/ በባንክ በተመሰከረ ሲፒኦ ከጨረታው ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ የሚችል።
  6. ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ለ21 ተከታታይ ቀናት ውስጥ በአ/ም ከፋ ፕ/ል መምሪያ ቢሮ ቁጥር 3 በመቅረብ የማይመለስ ብር 1500.00 /አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር / በመክፈል  የጨረታ ሰነድ እንድትገዙ እንገልፃለን ።
  7. ዋጋቸውን በማያሻማ መልኩ እንድታቀርቡ እናሳውቃለን ፡፡
  8. የጨረታ ሠነድ የሚገባው ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሲሆን በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በስራ ሰዓት ይሆናል፡፡
  9. የጨረታ ሣጥን የሚታሸገው በዕለቱ ከረፋዱ 4፡00 ሲሆን የሚከፈተው 4፡30 በከተማው በፋ ፕ/ል/መምሪያ ይሆናል፡፡
  10. ውል ማስከበሪያ ማስያዝ የሚችል፣
  11. ተጫራቾቹ ጨረታ ዶክምንት (አንድ) ቴከኒካል ኦርጅናልና 2(ሁለት) ቴክኒካል ኮፒና 1(አንድ) ፋይናንሻል ኦርጅናልና 2(ሁለት) ፋይናንሻል ኮፒ እንዲሆን CPO እያንዳንዱ በተለያዩ በታሸገ ፖስታ አድርው በእናት ፖስታ አሽገው ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  12. የዕቃው መጠን በሰነዱ ላይ በተገለፀው መሠረት በ20% ሊጨምርም ሆነ ሊቀንስ ይችላል፡፡
  13. ተጫራቾቹ ጨረታ ዶክምንት (አንድ) ቴክንካል ኦርጅናልና 2(ሁለት) ቴክኒካል ኮፒና 1(አንድ) ፋይናንሻል ኦርጅናልና 2(ሁለት) ፋይናንሻል ኮፒ እንዲሁን CPO እያንዳንዱ በተለያዩ በታሸገ ፖስታ አድርገው በእናት ፖስታ አሽገው ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  14. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡

ለተጨማሪ ማብራሪያ፡-0468 81 2389/ 046881 4353/046881 4619

በደቡብ ክልል የጋሞ ዞን አ/ም  ከተማ ፋ/ፕ/ል/መምሪያ


Tender details

  • Deadline: 2026-09-21
  • Bid closing time: 10:00
  • Bid closing (note): ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-09-21 10:30
  • Bid opening (note): ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት
  • Region: South Ethiopia Regional State
  • Publishing entity: የአርባ ምንጭ ከተማ ፋይናንስ እና ፕላን ልማት መምሪያ
  • Bid bond: 70,000.00 ብር ለእያንዳንዱ ሎት
  • Bid document price: 1500.00 ብር
  • Published on: Addis Zemen (Aug 30, 2026)
  • Posted at: 2026-08-31T09:12:39.000Z
← Back to all tenders