Materials
የአጋዝያን ቁ.3 2ኛ ደ/ት/ቤት አላቂ የት/ት እቃዎችን፣ አላቂ የጽዳት እቃዎችን፣ የደንብ ልብስ፣ የቢሮ እቃዎች፣ የፎቶ ኮፒ ቀለሞች እና የስፖርት እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
MaterialsEducation and TrainingStationery
Addis Ababa
More tags
Office Supplies and ServicesCleaning and Janitorial Equipment and ServiceTextile, Garments and UniformsTextile, Garment and LeatherShoes and Other Leather ProductsEquipment and AccessoriesElectrical, Electromechanical and ElectronicsComputer and AccessoriesIT and TelecomOffice Machines and AccessoriesSport Materials and EquipmentOffice FurnitureFurniture and FurnishingHouse FurnitureAmharic2merkatoAgaziyan No.3 Secondary School
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 01/2109 ዓ.ም.
የአጋዝያን ቁ.3 2ኛ ደ/ት/ቤት በ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት የሚከተሉት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- አላቂ የት/ት እቃዎችን፣
- አላቂ የጽዳት እቃዎችን፣
- የደንብ ልብስ፣
- የቢሮ እቃዎች፣
- የፎቶ ኮፒ ቀለሞች፣
- የስፖርት እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚህም መሰረት በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን ሁኔታዎች በቅድሚያ ማሟላት ይኖርባቸዋል።
- በተሰማሩበት የሥራ መስክ የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውና ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡ እንዲሁም የንግድ መለያ ቁጥር (Tin number) ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- በመንግሥት ግዥ ኤጀንሲ የንግድ ምዝገባ ማስረጃ ያላቸውና በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ።
- የቫት ተመዝጋቢ ለመሆናቸው የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- በመንግሥት ጨረታ ላይ የመሳተፍ ጊዜ ያላለፈበት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚያገለግሉ የሚጫረቱበትን የዕቃ ዋጋውን ብር 10,000.00/አስር ሺህ ብር/ በጽሕፈት ቤቱ ስም የተዘጋጀ /ሲፒኦ/ወይም በጽሕፈት ቤቱ ፋይናንስ በካሽ በማስያዝ ማረጋገጫውን ከመወዳደሪያው ሰነዶቻቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ማንኛውም ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች ናሙና ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- በጨረታው አሸናፊ ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ 10% ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- የምታስገቡቸው ሰነዶች ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ ሊኖረው አይገባም፣ስርዝ ድልዝ ያለው ሰነድ ውድቅ ነው የሚሆነው።
- የጨረታው ተሳታፊዎች የሚያቀርቡበትን የጨረታ ሰነድ በታሸገ ኤንቨሎፕ ኦርጂናሌና ኮፒ በማድረግ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- በሚሸጠው የጨረታ ሰነድ ላይ የሚገለፅ የእቃ ብዛት የመጨመርም ሆነ የመቀስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅተው የሚሰሩ ነጋዴዎች የድጋፍ ደብዳቤ ስታመጡ ደብዳቤው በጽ/ቤቱ ኃላፊ ቲተርና ፊርማ ተፈርሞ ማምጣት ግዴታ ነው።
- ከላይ የተጠቀሱት እቃዎች ዝርዝር የሚያሳውቅና የግዥ መመሪያ የያዘ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00/ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ፋ/ግ/ን/አ/ጽ/ቤት ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ዝርዝር የተጻፈ ሰነድ በአጋዝያን ቁ.3 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፋይናንስ ግዥና ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 1 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባችኋል፡፡ ጋዜጣው በወጣበት በ11ኛው /በአስራ አንደኛው የሥራ ቀን ጨረታው በዕለቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ 4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአጋዝያን ቁ.3 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፋይናንስ ግዥና ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 1 ይከፈታል፡፡ መሥሪያ ቤቱ የተሻለ የግዥ ዘዴ ካገኘ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው መሰረዝ ይችላል።
አድራሻ፡- ጎጃም በረንዳ /ሀግቤስ/ አቢሲኒያ ባንክ አጠገብ
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር፡- 0111-11-01-23 /0111-11-42-10 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
በአራዳ ክፍል ከተማ ት/ጽ/ቤት የአጋዝያን ቁ.3 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
የፋይናንስ ግዥና ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የሥራሂደት
Tender details
- Deadline: 2026-09-16
- Bid closing time: 10:00
- Bid closing (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው /በአስራ አንደኛው/ የሥራ ቀን ጨረታው በዕለቱ 4፡00 ሰዓት
- Bid opening: 2026-09-16 10:30
- Bid opening (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው /በአስራ አንደኛው/ የሥራ ቀን ጨረታው በዕለቱ 4፡30 ሰዓት
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Agaziyan No.3 Secondary School
- Bid bond: 10,000.00 ብር
- Bid document price: 200.00 ብር
- Published on: Addis Zemen (Sep 04, 2026)
- Posted at: 2026-09-04T08:51:27.000Z