Stationery

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ፋይናንስ ፅ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት የሚያስፈልጉ የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ፋይናንስ ፅ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት የሚያስፈልጉ የተለያዩ ዕቃዎችን በግዥ መለያ ቁጥር 01/2019 ማለትም

  • አላቂ የቢሮ ዕቃ፣
  •  የፅዳት ዕቃዎች፣
  •  ደንብ ልብስ፣
  •  ህትመት አገልግሎት፣
  • የመኪና ኪራይና ትራንስፖርት አገልግሎት፣
  •  የኮምፒውተር ጥገና የሼልፍ የወንበር ጠረጴዛ ጥገና፣ ቋሚ ዕቃ፣
  • የዘር ግዥ፣
  • የመስተንግዶ አገልግሎት፣
  • የእንስሳ የህክምና ዕቃዎች፣
  • የጉልበት አገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

 በመሆነም ከዚህ በታች ያለው መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች መወዳደር ትችላላችሁ።

  1.  በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድና የዘመኑ ዓ/ም የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና ቫት ተመዝጋቢ የሆናችሁ
  2. ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው ዕቃዎች በሙሉ ናሙና ማቅረብ ይጠበቅባችኋል። ናሙናው ማቅረብ ለማይችሉባቸው ዕቃዎች ብቻ በፎቶ የተደገፈ መሆን አለበት ናሙናዎቹም ጨረታ ከመከፈቱ በፊት ማስገባት አለባቸው እንዲሁም ያስገባቹሃቸውን ናሙናዎች እስከ 6 ወር ድረስ መልሰው ካልወሰዱ ለመንግስት ገቢ ይሆናል።
  3.  የመንግስት ግዥ አስተዳደር የግዥ አቅራቢነት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል
  4. በስራ ዕድል የተደራጁ ነጋዴዎች ባመረቱበት ምርት ወይም እሴት ተጨማሪ ባደረጉበት ብቻ ልዩ ተጠቃሚ የምናስተናግድ መሆኑን እያሳወቅን ወረዳው ብቃት ያላቸውን እና በመስኩ የተደራጁ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
  5. አንዱ በሌላ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችልም እና ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች ለእያንዳንዱ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል።
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10 ቀን ድረስ በመንግስት የስራ ሰዓት ለእያንዳንዱ የጨረታ አይነቶች በሎት የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ዋጋ 300 በመክፈል በን/ስ/ላ/ክ/ከ/05/ፋይናንስ ፅ/ቤት ግዥ ቡድን ቢሮ ቁጥር 103 ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  7. ጨረታው በ10 ቀን 11፡30 ሰዓት ታሽጎ በማግስቱ ማለትም 11 ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡00 በወረዳው አዳራሽ ይከፈታል። የመክፈታ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል።
  8. የዘገየ ጨረታና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም። አሸናፊ ተጫራቾችን ያሸነፉዋቸውን ዕቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መ/ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
  9. የትራንስፖርት አገልግሎት ለምትወዳደሩ ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፈቃድ እና ሊብሬ ማስያዝ ይኖርባቹሃል ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት ለተወዳደሩባቸው ዕቃዎች ናሙና ማቅረብ ሲኖርባቸው ለቋሚ ዕቃ በቀረበው ፍላጎት መግለጫ መሰረት መወዳደር ይጠበቅባቸዋል።

ተጫራቾችን የጨረታ ማስከበሪያ ከታች በሰንጠረዥ ለእያንዳንዱ ሎት ለየብቻ መሰረት በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ መስያዝ አለባቸው ሲፒኦ ከኦርጅናል ሰነድ ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት።

.

የጨረታው አይነት

ሎት

ጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ

1

አላቂ የቢሮ ዕቃዎች

ሎት 1

23,350

2

የፅዳት ዕቃዎች

ሎት 2

19,000

3

ደንብ ልብስ

ሎት 3

19,800

4

የህትመት አገልግሎት

ሎት 4

7,000

5

የመኪና ኪራይና ትራንስፖርት አገልግሎት

ሎት 5

4,000

6

የኮምፒውተር ጥገና የሼልፍ የወንበርና የጠረጴዛ ጥገና

ሎት 6

6,000

7

ቋሚ ዕቃ

ሎት 7

20,000

8

የዘር ግዥ

ሎት 8

6,000

9

የመስተንግዶ አገልግሎት

ሎት 9

19,314

10

የእንስሳ ህክምና ዕቃዎች

ሎት 10

1,200

11

የጉልበት አገልግሎት

ሎት 11

3,500

አድራሻ ን/ስ/ላ/ክ/ከ/ቄራ አልማዝዬ ሜዳ /ከ42 መዝናኛ ወረድ ብሎ ወ05 ፋይናንስ ፅ/ቤት

ስልክ ቁጥር፡- 011-88-83-40

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 05 ፋይናንስ ፅ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-09-15
  • Bid closing time: 17:30
  • Bid closing (note): ይህ የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ቀን 11፡30 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-09-16 10:00
  • Bid opening (note): ይህ የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11 ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 05 ፋይናንስ ፅ/ቤት
  • Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
  • Bid document price: 300.00 ብር ለእያንዳንዱ
  • Published on: Addis Zemen (Sep 06, 2026)
  • Posted at: 2026-09-07T09:13:37.000Z
  • Source: 2merkato
← Back to all tenders