Vehicle and Machinery Sale
አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ ተሽከርካሪ ባለበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Vehicle and Machinery SaleSales, Disposals and ForeclosureVehicle and Machinery Foreclosure
Addis Ababa
More tags
Description
በድጋሚ የወጣ የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
አቢሲንያ ባንክ /አማ/ ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውን እና በሠንጠረዡ ውስጥ የተመለከተውን ተሽከርካሪ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 ለባንኮች በተሰጠዉ ስልጣን መሠረት ንብረቱ ባለበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል:: በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የጨረታ መነሻ ዋጋውን ¼ (አንድ አራተኛ) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በአቢሲንያ ባንክ አማ ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
- የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ከፍሎ በጨረታ ያሸነፈበትን ንብረት መረከብ ይኖርበታል:: በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል:: በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል።
- ተበዳሪው /መያዣ ሰጪው/ በሐራጁ ቀን እና ሰዓት በቦታው መገኘት ይችላሉ:: ነገር ግን ባይገኙ ሐራጁ በሌሉበት ይካሄዳል::
- የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን፣ ግብር ፣ በሽያጩ ዋጋ ላይ የሚታሰብ የተጨማሪ እሴት ታክስ 15% እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውም ወጪዎችን ይከፍላል።
- ተሽከርካሪውን በሥራ ሰዓት ፕሮግራም አስይዞ መጎብኘት ወይም ማየት ይቻላል።
- በባንኩ የብድር ፖሊሲ እና መመሪያ መሰረት መስፈርቱን ለሚያሟላ የጨረታው ከፍተኛ ዋጋ አቅራቢ /አሸናፊ/ ባንኩ ከፊል ብድር ሊያመቻች ይችላል።
- የጨረታው ቦታ አዲስ አበባ ከተማ፣ ቂርቆስ ክ/ከተማ፣ ለገሀር በሚገኘው የአቢሲንያ ባንክ ኢማ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ B 4ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የፎርክሎዠርና ዴት ሊቲጌሽን ዲቪዥን ለጨረታ ባዘጋጀው ክፍል ውስጥ ነው።
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011 515 0711 ወይም 011 515 1153 በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
- ባንኩ የተሻለ አማራጭ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
|
የተበዳሪው ስም |
የመያዝ ሰጪው ስም |
የተሸከርካሪው ዓይነትና የተሰራበት ዘመን |
የሰሌዳ ቁጥር
|
የሻንሲ ቁጥር
|
የሞተር ቁጥር
|
የተሽከርካሪዉ ሞዴል
|
የጨረታ መነሻ ዋጋ ብር |
ጨረታዉ የሚካሄድበት ቀን |
የምዝገባ ሰዓት
|
የጨረታ ሰዓት
|
|
አቶ ደመላሽ ታደሰ ዓሊ |
ተበዳሪው |
የመስክ ተሸከርካሪ (ጃፓን ቶዮታ / Toyota Landcruiser V8 VXR/) (እ.ኤ.አ 2013) |
አአ-02-B78246 |
JTMHX05J2 E4061303 |
1UR0399671 |
URJ200L- GNTNKV |
12,141,740.00
|
መስከረም 12 ቀን 2019 ዓ.ም |
4:30-5:30 |
5:30-6:00
|
Tender details
- Deadline: 2026-09-22
- Bid closing time: 12:00
- Bid opening: 2026-09-22 12:00
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Bank of Abyssinia S.C.
- Buyer address: Addis Ababa Ethiopia
- Bid bond: 25%
- Published on: Reporter (Sep 06, 2026)
- Posted at: 2026-09-07T14:35:07.000Z
- Source: 2merkato