Stationery
በጂማ ዞን የሸቤ ሶንቦ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የተለያዩ የእቃ አይነቶች በግልጽ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
StationeryOffice Supplies and ServicesOffice Furniture
Oromia
More tags
Furniture and FurnishingHouse FurnitureGeneratorsEnergy, Power and ElectricityShoes and Other Leather ProductsTextile, Garment and LeatherTextile, Garments and UniformsEquipment and AccessoriesElectrical, Electromechanical and ElectronicsComputer and AccessoriesIT and TelecomOffice Machines and AccessoriesTri Wheeler, Motorcycles and Bicycles PurchaseSpare Parts and Car Decoration MaterialsCleaning and Janitorial Equipment and ServiceAmharic2merkatoJimma Zone Shebe Sonbo Woreda FEDB
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
በጂማ ዞን የሸቤ ሶንቦ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የእቃ አይነቶች በግልጽ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ፡-
- የጽሕፈት መሣሪያና አላቂ ዕቃዎች
- ፈርኒቸር
- ጀኔሬተር
- የደንብ ልብስ
- የኤሌክትሮኒከስ እቃዎች
- ሞተርሳይክል
- የመኪና ጎማ
ስለዚህ በዚህ ጨረታ ላይ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባችኋል።
- ተጫራቾች በዘርፉ ሕጋዊ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ፍቃድ ያሳደሱ ስለመሆናቸው ማስረጃቸውን ኦሪጅናልና ፎቶኮፒ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታከስ /VAT እና TIN No ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ሰርተፍኬት ኦሪጅናልና ፎቶ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባችኋል።
- ተጫራቾች በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸው ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚውል ለእያንዳንዱ የዕቃ ዓይነት ብር 20000 ሕጋዊነቱ ከተረጋገጠ ባንክ በ CPO ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ለዚህ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ከሸቤ ሶንቦ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የማይመለስ 200 ብር በመክፈል ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ በ 15 የሥራ ቀናት ውስጥ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች አስፈላጊውን ሰነድ በሙሉ ፎቶ ኮፒውን በአንድ ፖስታ ውስጥ ከተው ኦሪጅናሉን ደግሞ በሌላ አንድ ፖስታ ውስጥ ከተው, technical document በአንድ ፖስታ ውስጥ ከተው ባጠቃላይ በ 3 ፖስታዎች ውስጥ ከተው, ፖስታዎቹን በሰም አሽገው ላዩ ላይ ፈርመውና ማሕተም አድርገውበት ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ እስከ 15ኛው የሥራ ቀን 11፡00 ሰዓት ድረስ መከተት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው የሚከፈተው በ16ኛው የሥራ ቀን በ4፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች (ሕጋዊ ወኪሎቻቸው) በተገኙበት በመሥሪያ ቤታችን የግዥ ከፍል (ቢሮ ቁጥር 3) የሚከፈት ይሆናል።
- የተጫራች ሰነዶች ቀርቦ ተጫራች በአካል ባይገኝም ጨረታው ይከፈታል።
- አሸናፊ ሆኖ የተገኘ ተወዳዳሪ የሚታዘዘውን ዕቃ በሙሉ ወጪውን ችሎ እስከ መሥሪያ ቤታችን ድረስ የሚያቀርብ ይሆናል።
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የሸቤ ሶንቦ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-09-28
- Bid closing time: 17:00
- Bid closing (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 15ኛው የሥራ ቀን 11፡00 ሰዓት
- Bid opening: 2026-09-29 10:00
- Bid opening (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው የሥራ ቀን በ4፡00 ሰዓት
- Region: Oromia
- Publishing entity: Jimma Zone Shebe Sonbo Woreda FEDB
- Bid bond: 20000 ብር ለእያንዳንዱ የዕቃ ዓይነት
- Bid document price: 200.00 ብር
- Published on: Addis Zemen (Sep 11, 2026)
- Posted at: 2026-09-12T08:29:47.000Z
- Source: 2merkato