Stationery

የኢትዮጵያ ፖስታ የጽህፈት መሳሪያ፣ የጽዳት ዕቃዎች፣ የተሽከርካሪ መኪና ጐማዎች እና የመኪኖች ብራንዲንግ ቀለም ቅብ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

 የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር የኢ/ፖ/አ/ድ ግጨ 03/2019 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ፖስታ የጽህፈት መሳሪያ ፣ የጽዳት ዕቃዎች ፣ የተሸከርካሪ ጐማዎች እና ፣ የመኪኖች ብራንዲንግ ቀለም ቅብ፣ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ በድርጅቱ ዋናው መሥሪያ ቤት ፋይናንስ ዲፖርትመንት 2ኛ ፎቅ የማይመለስ ብር 500.00/አምስት መቶ ብር/ በየሎቱ በመክፈል ለጨረታው የተዘጋጀውን የጨረታ ሠነድ ግዥ ከፍል ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ግዥው እንደሚከተለው በሠንጠረዥ ተቀምጧል፡፡

ተራ ቁ.

ሎት

የጨረታው አይነት

በየሎቱ በሁኔታዎች ላይ ያልተመሠረተ የጨረታ ማስከበሪያ(CPO)

1

ሎት 01

የጽህፈት መሳሪያዎች

100,000.00

2

ሎት 02

የጽዳት ዕቃዎች

100,000.00

3

ሎት 03

የተሸከርካሪ መኪና ጐማዎች

100,000.00

4

ሎት 04

የመኪኖች ብራንዲንግ ቀለም ቅብ

100,000.00

ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ፡-

  1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ
  2. ታከስ ክሊራንስ የታደሰ
  3. የግብር ከፋይ ሠርተፍኬት (Tin certificate)
  4. የቫት ሠርተፍኬት (የተጨማሪ እሴት ታክስ ሠርተፍኬት)
  5. ከሎት 1- 3 ለተዘረዘሩት የጨረታ አይነቶች የፋይናንሻል እና ቴክኒካል ሠነድ ኦርጅናል እና ኮፒ ለየብቻው በማድረግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራቾች ናሙና ባላቀረቡበት እቃ ላይ ዋጋ መስጠት የለባቸውም ።
  6. ለመኪኖች ብራንዲንግ ቀለም የፋይናንሻል እና ቴክኒካል ሠነድ ኦርጅናል እና ኮፒ ለየብቻው በማድረግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  7. ሌሎች በጨረታ ሠነዱ ላይ የተገለፁትን ሠነዶች አሟልተው ማቅረብ አለባቸው
  8. ተጫራቾች በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ በየሎቱ የ100,000.00(አንድ መቶ ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  9. ጨረታው መስከረም 20 ቀን 2019 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 9፡00 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል፡፡
  10. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  11. ሲፒኦ /CPO/ ሲያሠሩ “የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት “Ethiopian postal Service enterprise” በማለት ማሰራት ይኖርባቸዋል፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09-11-73-00-62

የኢትዮጵያ ፖስታ


Tender details

  • Deadline: 2026-09-30
  • Bid closing time: 14:30
  • Bid opening: 2026-09-30 15:00
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Ethiopost
  • Buyer address: Addis Ababa, Ethiopia
  • Bid bond: 100,000.00 ብር ለእያንዳንዱ ሎት
  • Bid document price: 500.00 ብር ለእያንዳንዱ
  • Published on: Addis Zemen (Sep 14, 2026)
  • Posted at: 2026-09-14T08:15:11.000Z
  • Buyer website: https://ethio.post/
  • Source: 2merkato
← Back to all tenders