Cleaning and Janitorial Equipment and Service

የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ለ2019ዓ.ም በጀት ዓመት በስሩ ለሚገኙ ዳይሬከቶሬቶቸ አገልግሎት የሚሰጥ (እስቴሽነሪ)፣ አላቂና ከፊል አላቂ እና የጽዳት እቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር የድ/ዳ/አስ/ስ/ክ/ቢ/03/2019 ዓ.ም

የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ለ2019ዓ.ም በጀት ዓመት በስሩ ለሚገኙ ዳይሬከቶሬቶቸ አገልግሎት የሚሰጥ (እስቴሽነሪ)፣ አላቂና ከፊል አላቂ እና የጽዳት እቃዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ሁሉ ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች በሟሟላት መወዳደር ይችላሉ።

1. ተጫራቾች የቫት ተመዝጋቢ፣ በስራው መስክ ህጋዊና የታደሠ የንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉትነ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፣

2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለዕያንዳዱ ሰነድ 5000.00 (አምስት ሺ ብር) በባንክ በተመሠከረ ቼክ (CPO) ከጨረታ ሠነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፣

3. ከባለስልጣን መስሪያ ቤት ለ2019 በጀት አመት የተሰጠ የአቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፡፡

4. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የግዢና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ከፍል ቢሮ ቁጥር 19 መግዛት ይችላሉ፡፡

5. ተጫራቾች ላሸነፉባቸው አገልግሎት የጠቅላላ ዋጋ 10% በውል ማስከበሪያነት ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

6. የጨረታው ሳጥን የሚዘጋው በ16ኛ ቀን በአለቱ በ 3፡30 ሠዓት ሆኖ ጨረታው የሚከፈተው በተመሳሳይ ቀን 4፡00 ሠዓት ተጯራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኮሌጁ የግዢ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የስራ ሂደት ቢሮ ውስጥ ይከፈታል፡፡

7. ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብት አለው፡፡

8. በጨረታ ሰነዱ ላይ ዋጋ ለቀረበበት እቃዎችን ሳምፕል(ናሙና) ማቅረብ የሚችል፡፡

9.የስራ ውሉ እንዲቋረጥ አስገዳጅ ሁኔታ ካልተፈጠረ በስተቀር ውሉ እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ሰኔ 30/2019ዓ.ም ድረስ ይቆያል፡

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0993 861 940 / 0993 439 544 ወይም 0968 326 118 በመደወል ማብራሪያ መጠየቅ ይችላሉ፡፡


Tender details

  • Deadline: 2026-10-01
  • Bid closing time: 12:00
  • Bid closing (note): ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ቆይቶ በ16ኛ ቀን በ3፡30 ሠዓት
  • Bid opening: 2026-10-01 12:00
  • Bid opening (note): ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ቆይቶ በ16ኛ ቀን በ4፡00 ሠዓት
  • Region: Dire Dawa
  • Publishing entity: Dire Dawa Administration Jobs and Skills Office
  • Bid bond: 5,000.00 ብር ለእያንዳንዱ ሰነድ
  • Bid document price: 500.00 ብር
  • Published on: Melekite Dire (Sep 16, 2026)
  • Posted at: 2026-09-18T08:44:50.000Z
  • Source: 2merkato
← Back to all tenders