በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ በከኒሳ ጤና ጣቢያ ለ2018 በጀት አመት ልዩ ልዩ ዕቃዎችን መግዛት ይፈልጋል

Description

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ በከኒሳ ጤና ጣቢያ ለ2018 በጀት አመት የሚያስፈልጉ እቃዎች በግዥ መለያ ቁጥር 001/2018 ማለትም

  • በሎት 1 ቋሚ እቃዎች
  • በሎት 2 የጥገና (የህንፃ መሳሪያ) እቃዎች
  • ሎት 3 አላቂ የቢሮ እቃዎች
  • ሎት 4 አላቂ የፅዳት እቃዎች
  • ሎት 5 ህትመቶች
  • ሎት 6 የጥገና እና የጉልበት ስራ እና ሌሎችም በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ የጨረታ ማስከበሪያ ብር

ሎት ቁጥር

የጨረታው አይነት

ጨረታ ማስከበሪያ የብር መጠን

ምርመራ

ሎት 1

ቋሚ እቃዎች

15,000

በተቋሙ ስፔስፍኬሽንና በፎቶ

ሎት 2

የጥገና (የህንፃ መሳሪያ)እቃዎች

10,000

ናሙና የሚቀርብ

ሎት 3

አላቂ የቢሮ እቃዎች

10,000

ናሙና የሚቀርብ

ሎት 4

አላቂ የማዳት እቃዎች

5.000

ናሙና የሚቀርብ

ሎት 5

ህትመቶች

3,000

በመ/ቤቱ ናሙና

ሎት 6

የጥገና እና የጉልበት ስራ

5,000

የስራውን ሰነድ በመግዛት

በባንክ በተረጋገጠ ሰነድ (CPO) ከጨረታ ሰነዱ ጋር በፓስታ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ብቃት ያላቸውንና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት፡-

1 በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ የቲንና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣ የአቅራቢ ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።

2 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ብር 150 (አንድ መቶ ሃምሳ ብር) ብቻ በመክፈል ሰነድን ጤና ጣቢያ ፋይናንስ ቢሮ ቀርበው መግዛት ይችላሉ።

3 የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ታተሞ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ቀን እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ አየር ላይ ውሎ በ11ኛው ቀን አጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኘበት በጤና ጣቢያው መሰብሰቢያ አዳራሽ ጨረታው ይከፈታል፡፡ ነገር ግን የጨረታው መክፈቻ ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም በዓል ቀን ከዋለ በቀጣይ የስራ ቀን በተባለው ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።

4 ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኢንቨሎፕ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 (አስር) የስራ ቀናት ጤና ጣቢያው ግቢ ውስጥ ግዥ ቡድን ቢሮ ለጨረታ በተዘጋጀ ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

5 ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት የመ/ቤቱ ፍላጎት (ስፔስፍኬሽን) ለሚያስፈልጋቸው ሎቶች በጥንቃቄ በስፔስፍኬሽኑ መሰረት ብቻ መሞላት አለበት፡፡ ናሙና ለሚያስፈልጋቸው ሎቶች ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

6 ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን እቃዎች ለአያንዳንዱ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል።

7 የዘገየ ጨረታና የጨረታው መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም።

8 አሸናፊ ተጫራቾች ያሽነፍባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፓርት ግዥ ፈፃማው መስሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።

9 ጤና ጣቢያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ በከኒሳ ጤና ጣቢያ ወረዳ 02 ፊት ለፊት

ስልክ ቁጥር 0996 943434

በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት በከኒሳ ጤና ጣቢያ


Tender details

  • Deadline: 2026-04-22
  • Bid closing time: 17:30
  • Bid closing (note): የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ታተሞ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ቀን እስከ 11፡30 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-04-23 12:00
  • Bid opening (note): የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ታተሞ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን አጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ወረዳ 02 በከኒሳ ጤና ጣቢያ
  • Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
  • Bid document price: 150.00 /አንድ መቶ ሀምሳ ብር/
  • Published: Apr 11, 2026
  • Posted at: 2026-04-11T08:21:39.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders