የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጅግጅጋ ቅ/ፅ/ቤት እስከ 2 አመት የሚቆይ ቢሮ ኪራይ ጨረታ የግዥ ዘዴ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

ብሔራዊ ግልጽ ጨረታ  ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር፡ ኢስአ/ግጨ/jጅግ/001/2018

መ/ቤታችን በ2018 በጀት ዓመት ከዚህ በታች በሠንጠረዥ የተመለከቱትን ከመንግሥት በተፈቀደለት በጀትና በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ የግዥ ዘዴ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

ተ.ቁ

የግዥው ዓይነት

የጨረታ ሠነድ መግዥያ ዋጋ መግለጫ (የማይመለስ)

የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ወይም የባንክ ዋስትና መጠን በብር

1

እስከ 2 አመት የሚቆይ ቢሮ ኪራይ ጨረታ

200.00

5,000.00

በመሆኑም ተጫራቾች፡-

  1. የጨረታ ሰነዱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጅግጅጋ ቅ/ጽ/ቤት ግዥና ፋይናንስ በመምጣት 200 ብር ከፍለው መውሰድ ይችላሉ።
  2. ባለቤትነት ይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፍኬት ወይም የቲኦቲ ተመዝጋቢ የሆነ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ሰርተፊኬት /TIN number/ እና በጨረታ ላይ ለመሳተፍ የሚያስችል ጨረታ ከመከፈቱ በፊት የተሰጠ የታክስ ክሪላንስ ሰርተፍኬት ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
  3.  በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጅግጅጋ ቅ/ጽ/ቤት ስም የተዘጋጀ፣ በቅድመሁኔታ ያልተገደበ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የባንክ ጋራንቲ ወይም CPO ብር 5,000 ከመጫረቻ ሠነድ ጋር ተያይዞ መቅረብ ይኖርበታል።
  4. ተጫራቾች የሚጫረቱበት የአገልግሎት ግዥ ለተጫራቾች በሚሸጠዉ የጨረታ ሰነድ ከፍል 6 ላይ ከተመለከተዉ የቴክኒክ ፍላጎት ጋር መጣጣም ይኖርበታል።
  5. ሠነዳቸውን አንድ ኦሪጅናልና አንድ ኮፒ ለየብቻው በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ እስከ መጋቢት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡ ጨረታው በዚሁ ቀን 8:00 ሰዓት ተዘግቶ ከዚሁ ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ከቀኑ 8:30 ሰዓት ጅግጅጋ ስታቲስቲክስ ቅ/ፅ/ቤት ቢሮ ይከፈታል፡፡ ሆኖም ይህ ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም በበዓላት ቀን ከዋለ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተጠቀሰው ሰዓት የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ይሆናል።
  6. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ ለመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ ስልክ ቁጥር 0910144705/0910866265

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ጅግጅጋ ቅ/ፅ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-05-05
  • Publishing entity: Ethiopian Statstics Service Jigjiga Bureau
  • Bid bond: 5,000.00 ብር
  • Bid document price: 200.00 ብር
  • Published: Apr 11, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders