ጊፍት ሪል ስቴት (Gift Real Estate) በአዲስ አበባ ቦሌ በሚገኘው ህንጻው ውስጥ የሚገኙ ዋና ዋና የመሬት ላይ ሱቆችን እና ክፍት የንግድ ቦታዎችን በሊዝ ለማከራየት ብቁ የሆኑ ተጫራቾችን በጨረታ እንዲወዳደሩ ይጋብዛል

Description

የሊዝ ጨረታ ማስታወቂያ

የንግድ ቦታ ኪራይ | የማጣቀሻ ቁጥር (Ref, No) GR/RE/2018/001

ጊፍት ሪል ስቴት (Gift Real Estate) በአዲስ አበባ ቦሌ በሚገኘው ህንጻው ውስጥ የሚገኙ ዋና ዋና የመሬት ላይ ሱቆችን እና ክፍት የንግድ ቦታዎችን በሊዝ ለማከራየት ብቁ የሆኑ ተጫራቾችን በጨረታ እንዲወዳደሩ ይጋብዛል። እነዚህ ምርጥ ቦታዎች ለቅንጡ ቡቲኮች፣ ለዕቃ ማሳያ ማዕከላት (showrooms)፣

ለካፌዎች ወይም ለሬስቶራንቶች ተስማሚ ናቸው፡፡

1. የሊዝ ውል ሁኔታዎች እና የአሸናፊዎች አመራረጥ

  • የመነሻ የሊዝ ዋጋ በወር በአንድ ካሬ ሜትር 2,200 የኢትዮጵያ ብር (ተጨማሪ እሴት ታክስን ሳይጨምር)።
  • የአሸናፊዎች መምረጫ መስፈርት ተጫራቹ የሚሰጠው ከፍተኛ የዋጋ አቅርቦት ላቀረበ እና ረጅሙን የቅድመ ክፍያ ጊዜ ለፈጸመ ተጫራች ይሆናል።
  • የጨረታ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ)፦ ተጫራቾች 100,000 የኢትዮጵያ ብር በጥሬ ገንዘብ ወይም በሲ.ፒ.ኦ (CPO) በጊፍት ሪል ስቴት ኃ.የተ.የግ.ማ (Gift Real Estate PLC) ስም ማስያዝ አለባቸው።
  • የሰነድ ክፍያ የለም የሚገዛ የጨረታ ሰነድ የለም፣ ፍላጎት ያላቸው አካላት የጨረታ ጥያቄያቸውን (proposal) ከላይ የተጠቀሱትን በመዘርዘር በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በቀጥታ ማቅረብ ይችላሉ።

2. የመወዳደሪያ መስፈርቶች

  • ለድርጅቶች የምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና የግብር ክሊራንስ።
  • ለግለሰቦች የታደሰ የታወቀ መታወቂያ (ID)።

3. አቀራረብ እና የጨረታ አከፋፈት

የጨረታ ጥያቄዎች በታሽገ ኤንቨሎፕ የማጣቀሻ ቁጥሩ ተጽፎባቸው ከዚህ በታች ወዳለው አድራሻ መቅረብ አለባቸው፦

  • የመቀበያ ጊዜ፦ ከሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም (Apr. 14, 2026) ጠዋት 3:00 ሰዓት ይጀምራል።
  • የመዝጊያ ቀን፦ ሚያዝያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም (April 24, 2026) ከሰዓት 10:00 ሰዓት።
  • ጨረታው የሚከፈትበት ጊዜ፦ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (April 25, 2026) ጠዋት 4:30 ሰዓት (ተጫራቾች በተገኙበት)፡: ቦታ ቦሌ፣ ጊፍት ሪል ስቴት ዋና መሥሪያ ቤት፣ 5ኛው ፎቅ፣ የጊፍት ፕሮፐርቲ ማኔጅመንት ቢሮ።

ጊፍት ሪል ስቴት ኃየተ.የግ.ማ ቦሌ፣ አዲስ አበባ | የስልክ ቁጥር +251930174112/+251989068814

ማሳሰቢያ፦ ድርጅቱ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።


Tender details

  • Deadline: 2026-04-24
  • Bid closing time: 16:00
  • Bid opening: 2026-04-25 10:30
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Gift Real Estate P.L.C.
  • Bid bond: 100,000.00 ብር
  • Published: Apr 12, 2026
  • Posted at: 2026-04-14T10:01:24.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders