የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ የኃይጅንና ሳንቴሽን ሥራዎችን ለማጠናከር የሚያገለግል የቆሻሻ ማስቀመጫ/DUST BIN/ በግልፅ ጨረታ የግዥ ዘዴ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል
Description
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ የኃይጅንና ሳንቴሽን ሥራዎችን ለማጠናከር የሚያገለግል የቆሻሻ ማስቀመጫ/DUST BIN/ በግልፅ ጨረታ የግዥ ዘዴ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል።
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች ለወዳደር የተጋበዙ መሆኑን እያሳወቅን፡-
- በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ሰርተፍኬት የሚያቀርቡ።
- ከላይ በተራ. ቁ 1-2 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸዉ ጋር አያይዘዉ ማቅረብ የሚችሉ።
- የሚገዛው ዕቃ ጠቅላላ ዋጋ ከ 200,000.00/ ሁለት መቶ ሺህ ብር / በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ የሆነና የቫት ሰርተፊኬት ኮፒ ማስያዝ አለበት።
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩት ጠቅላላ ዋጋ 2% በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና የሚያስይዝ፤ ሆኖም የጨረታ ማስከበሪያው ጠቅላላ ዋጋ ከ 500,000.00/አምስት መቶ ሽህ ብር/ መብለጥ የለበትም።
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን በታሸገ ፖስታ በማድረግ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት በ15 ተከታታይ ቀናት ዉስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን የፋይናንሻል ሰነድ ኦርጅናል እና ኮፒ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፤
- ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በ16ኛው ቀን 2018 ዓ.ም በ 8:30 ሰዓት ታሽጎ 9፡00 ሰዓት ይከፈታል። ሆኖም ዕለቱ የስራ ቀን ካልሆነ በተከታዩ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚታሸግና የሚከፈት ይሆናል።
- ሌሎች ተጫራቾች በሚያቀርቡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም።
- ቢሮው የግዥዉን መጠን እስከ 20% ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል።
- የጨረታዉ አሸናፊ የሆነ ድርጅት ያሸነፈውን የኃይጅን እና ሳኒቴሽን እቃዎች የጨረታ ሰነዱ ላይ በተቀመጠው ስርጭት (ድልድል መሰረት ለጤና ተቋማት ማቅረብ አለበት።
- በጨረታው የተወዳደረ ተጫራች የጨረታ ሰነዱን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር / በመክፈል ከቢሮው የሰነድ ሽያጭ ከፍል መውሰድ ይችላል።
- ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ስለ ጨረታዉ መረጃ ከፈለጉ አብክመ ጤና ቢሮ ስልክ ቁጥር 058-222-1127 በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይቻላል።
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጤና ቢሮ
Tender details
- Deadline: 2026-05-11
- Bid closing time: 14:30
- Bid closing (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን 2018 ዓ.ም በ 8:30 ሰዓት
- Bid opening: 2026-05-11 15:00
- Bid opening (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን 2018 ዓ.ም በ9:00 ሰዓት
- Region: Amhara
- Publishing entity: Amhara National Regional State Health Bureau
- Bid bond: 2%
- Bid document price: 500.00 ብር
- Published: Apr 26, 2026
- Posted at: 2026-04-27T09:54:25.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.