የድሬዳዋ ከተማ ጽዳት ውበት እና አረንጓዴ ልማት ኤጀንሲ በከተማው ውስጥ በሚሰጠው ስምሪት መሰረት በጽዳት ማህበራት ከቤት ለቤት የሚሰበሰበውን ደረቅ ቆሻሻ በተሽከርካሪ በመቀበል እስከ ቆሻሻ ማስወገጂያ ቦታ በማጓጓዝ የማስወገድ አገልግሎት መስጠት የሚፈልጉ ድርጅቶችን/ማህበራቶችን በጨረታ አወዳድሮ በኮንትራት ውል ለማሠራት ይፈልጋል
Description
የድሬዳዋ ከተማ ጽዳት ውበት እና አረንጓዴ ልማት ኤጀንሲ
ደረቅ ቆሻሻን በተሽከርካሪ በማጓጓዝ የማስወገድ አገልግሎት መስጠት ለሚችሉ በጽዳት አገልግሎት ዘርፍ ፈቃድ ላላቸው ተጫራች ማሕበራት/ድርጅት የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የድሬዳዋ ከተማ ጽዳት ውበት እና አረንጓዴ ልማት ኤጀንሲበከተማው ውስጥ በሚሰጠው ስምሪት መሰረት በጽዳት ማህበራት ከቤት ለቤት የሚሰበሰበውን ደረቅ ቆሻሻ በተሽከርካሪ በመቀበል እስከ ቆሻሻ ማስወገጂያ ቦታ በማጓጓዝ የማስወገድ አገልግሎት መስጠት የሚፈልጉ ድርጅቶችን/ማህበራቶችን በጨረታ አወዳድሮ በኮንትራት ውል ለማሠራት በመፈለጉ ይህንን የጨረታ ማስታወቂያ አውጥቶአል።
በዚሁ መሰረት በከተማ ጽዳትና ውበት አገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ ማሕበራት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶችን በማሟላት የጨረታ ሰነዱን በመግዛት በጨረታው ላይ መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
የተጫራቾች መመሪያ
- ተጫራቾች በከተማ ጽዳት እና ውበት ዘርፍ በማሕበር የተደራጁና ህጋዊ የታደሰ የስራ ፈቃድ ያላቸው የግብር ከፋይ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችልየዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- የቫት ከፋይ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ የሚያቀርቡ
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተቀመጡ መመሪያዎች፤ የመገምገሚያና ቴክኒካል መስፈርቶቹ የሚጠይቁትን ተዛማጅ ጉዳዮች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በድሬ ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰአት ከከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ፋ/ግ/ንብ/አስተዳደር ክፍል በመቅረብ የማይመለስ 300 ብር በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የገዙትን የጨረታ ሰነድ በሚገባ አንብበውና ተረድተው በመሙላት አንድ ኦሪጂናልና ሁለት ኮፒ የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ይህ ማስታወቂያ በድሬ ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት እስከ 21ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 3 ሰአት ድረስ የጨረታ ሰነዱን ከገዙበት ከከተማ ስራ ኣስኪያጅ ጽ/ቤት ፋ/ግ/ንብ/አስተዳደር ክፍል ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚመለስ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10000 / አስር ሺህ ብር / በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተመሰከረ ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ሳጥኑ ይህ ማስታወቂያ በድሬ ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት እስከ 22ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4:00 ሰአት ድረስ ክፍት ሆኖ ከቆየ በሁዋላ 4:00 በዛኑ ቀንና ሰአት ተዘግቶ ወዲያውኑ 4:30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የበለጠ መረጃዎችን ከሚገዙት የጨረታ ሰነድ ላይ መመልከት ይኖርባቸዋል
- አስፈላጊ የሆኑ ማብራሪያዎችን ከጽደትና ውበት ኤጀንሲ ቢሮ ወይም ከከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ፋ/ግ/ንብ/አስተዳደር ክፍል በመጠየቅ ማግኘት ይቻላል፡፡
- መ/ቤቱ የተሸለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብት አለው
Tender details
- Deadline: 2026-07-11
- Publishing entity: የድሬዳዋ ከተማ ጽዳት ውበት እና አረንጓዴ ልማት ኤጀንሲ
- Bid bond: 10,000.00 (አስር ሺ ብር)
- Bid document price: 300.00 ብር
- Published: Jun 17, 2026
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.