ወጋገን ባንክ አ.ማ. ንብረቶች በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Description
ቁጥር ወጋገን 021/2018
ወጋገን ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 መሰረት ከዚህ በታች የቀረቡትን የመያዣ ንብረቶች በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ
|
ተ.ቁ |
የተበዳሪው ስም |
ንብረት አስያዥ |
አበዳሪ ቅርንጫፍ |
የንብረቱ አድራሻ |
የቦታው ስፋት
|
የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ ቁጥር
|
የንብረቱ ዓይነት/የይዞታው ኣገልግሎት
|
የጨረታ መነሻ ዋጋ ብር
|
ጨረታ የሚከናወንበት ጊዜ |
|||
|
ከተግ/ክልል |
ክ/ከተማ/ከተማ/ዞን |
ቀበሌ/ወረዳ
|
ቀን
|
ሰዓት
|
||||||||
|
1 |
ማሕዮ ኢብራሂም |
ፀጉ አባዲ በርሀ |
ኢንኮደ
|
ትግራይ
|
መቐለ
|
ዓዲ-ሓቂ
|
199.1 ካ/ሜትር
|
2904/04/5968
|
መኖሪያ ቤት (G+2) ግንባታው 61/100 የተጠናቀቀ |
5,690,032.98
|
ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም |
ከጧቱ 3፡00-6:00 ሰዓት |
|
2 |
ንግስቲ ወላይ |
ገ/ጊዮርጊስ ገ/ህይወት |
መቐለ
|
ትግራይ
|
መቐለ
|
ሰሜን
|
380 ካ/ሜትር
|
661/29378
|
መኖሪያ ቤት ግንባታው 68/100 የተጠናቀቀ |
5,557,854.56
|
||
|
3 |
ገ/አናንያ ገ/ሚካኤል ካሕሳይ |
ተበዳሪዉ |
ሓወልቲ |
ትግራይ
|
መቐለ
|
ሓወልቲ |
358.8 ካ/ሜትር |
414/39545
|
መኖሪያ ቤት (G+1) |
12,354,248.58 |
ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም |
ከቀኑ 7:00-10፡00 |
|
ገ/አናንያ ገ/ሚካኤል ካሕሳይ ገ/ፃዲቅ
|
ሓወልቲ |
ትግራይ
|
መቐለ
|
ሓወልቲ |
161 ካ/ሜትር
|
12287/03/2948 |
የንግድ ህንፃ/ለቅይጥ አገልግሎት (B+G+4)
|
18,486,951.57
|
||||
|
4 |
ሰንራይዝ እንጅነሪንግ |
ተክለወይኒ ገ/ሄር |
ዓዲ ሓዉሲ |
ትግራይ
|
ዓድዋ
|
06 |
175 ካ/ሜትር |
638/99 |
መኖሪያ ቤት (G+1) ግንባታው 65/100 የተጠናቀቀ
|
3,616,679.68 |
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም |
ከጧቱ 3፡00-6:00 ሰዓት |
|
5 |
ደስታ አለማዮህ |
ተበዳሪው |
አፅቢ |
ትግራይ
|
አፅቢ |
አጽቢ |
500 ካ/ሜትር |
6/ዶ/65 |
የንግድ ህንጻ (G+3) ግንባታው 51/100 የተጠናቀቀ |
8,158,803.26
|
||
|
6 |
ተስፋአለም ታደሰ ፍስሃ |
ተበዳሪው |
አክሱም |
ትግራይ
|
አክሱም |
03 |
140 ካ/ሜትር |
1734/መም/2004 |
መኖሪያ ቤት (G+2) |
3,923,773.07
|
ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም |
ከጧቱ 3፡00-6:00 ሰዓት |
ማሳስቢያ
1. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የጨረታ መነሻ ዋጋ 1/4(አንድ አራተኛ) በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ (C.P.O) በወጋገን ባንክ አ.ማ ስም በማሰራት በጨረታው ዕለት በመቅረብና በመመዝገብ በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ።
2. የጨረታ አሸናፊ ከባንኩ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ከተሰጠው ቀን ጀምሮ ቀሪውን ገንዘብ በ15 /አስራ አምስት/ ቀናት ውስጥ አጠናቆ መክፈል ይኖርበታል። ባይከፍል ግን የሐራጁ ውጤት ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፤ ላላሸነፉት ተጫራቾች ግን ያስያዙት ሲፒኦ ወዲያዉኑ ይመለስላቸዋል።
3. በጨረታው አሸናፊ ለሆነ፤ የባንኩን የብድር ፖሊሲ፤ መመሪያ እና ቅድመ ሁኔታ ለሚያሟላ ተጫራች ባንኩ በውስጥ መመሪያ መሰረት ብድር ሊያመቻች ይችላል።
4. የተጫራቾች የምዝገባ ሰዓት፣ ከጧቱ 3፡00_4፡00 ሰዓት እና ከቀኑ 7፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ሲሆን ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ለእያንዳንዱ ንብረት የሚመደበው የጥሪ ሰዓት 30 ደቂቃ ብቻ ነው። ሆኖም የጨረታው መጠናቀቂያ ሰዓት ድረስ አሸናፊው ካልተለየ አሸናፊ እስኪለይ ድረስ ጨረታው ይቀጥላል።
5. በጨረታው የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ጨረታውን ካካሄደው ከባንኩ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ሊደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል።
6. ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል።
7. ጨረታው የሚካሄደው፡ ከተራ ቁ.1 እስከ 3 ድረስ የተዘረዘሩት ንብረቶች በባንኩ ቺፍ ሰሜን ሪጅናል ጽ/ቤት፤ ከተ.ቁጥር 4 እስከ 6 ድረስ የተጠቀሱት ንብረቶች አንደየቅደም ተከተላቸው በባንኩ ዓድዋ ኣክሱም አና አጽቢ ቅርንጫፎች ላይ የሚካሄድ ይሆናል።
8. ለሀራጅ ጨረታ የቀረቡትን ንብረቶች ለመጎብኘት የሚፈልግ ተጫራች የጨረታው ቀን ከመድረሱ በፊት ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በማስያዝ መጎብኘት ይችላል።
9. ተበዳሪው ብረት አስያዥ/ ወይም ሁለቱም በጨረታው ቀን እና ሰዓት በቦታው ላይ መገኘት ይችላሉ። ነገር ግን ተበዳሪው ንብረት አስያዡ/ በጨረታ ቀን እና ሰዓት በቦታው ባይገኝ ጨረታው በሌለበት ይካሄዳል። ከዚህ በተጨማሪ ጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች ወይም የተጫራቾች ህጋዊ ተወካዮች ብቻ ናቸው።
10. ማንኛውንም ለመንግስት ሊከፈል የሚገባውን ክፍያ ማለትም የተጨማሪ እሴት ታክስ ክፍያን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ የጨረታው አሸናፊ የሚከፍል ይሆናል።
11. ለበለጠ ማብራሪያ ወይም የጉብኝት ቀጠሮ ለማመቻቸት ወጋገን ባንክ አ.ማ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት 011-558-1837፣ የባንኩ ቺፍ ሰሜን ሪጅናል ጽ/ቤት፡ 034-241-5185/ 034-241-5186 የሽሬ ዲስትሪክት ጽ/ቤት 034-244 3685/ 034-244-4248 እና የዓድዋ ቅርንጫፍ፡ 034-771-4046/ 034_771_4043
12. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም።
ወጋገን ባንክ አ.ማ
Tender details
- Deadline: 2026-06-04
- Publishing entity: Wegagen Bank S.C.
- Bid bond: 25%
- Published: May 03, 2026
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.