የደ/ኢት/ክ/መ ፕላንና ልማት ቢሮ ለ2018 በጀት ዓመት ለቢሮው አገልግሎት የሚውሉ አላቂ ዕቃዎች፣ ሌሎች አላቂ ዕቃዎች፣ የፅዳት ዕቃዎችና ኤሌክትሮኒክሶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

የደ/ኢት/ክ/መ ፕላንና ልማት ቢሮ ለ2018 በጀት ዓመት ለቢሮው አገልግሎት የሚውሉ አላቂ ዕቃዎች፣ ሌሎች አላቂ ዕቃዎች፣ የፅዳት ዕቃዎችና ኤሌክትሮኒክሶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

በዚህም መሠረት ተጫራቾች፡-

  • የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥርና ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢየሆኑ እንዲሁም የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን ይጠበቅባቸዋል በተጨማሪ የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ሊኖራቸው ይገባል።
  • የጨረታ ማስከበሪያ ከሕጋዊ ባንክ CPO ወይም በካሽ ለ10,000 ከሚያቀርቡት ከዕቃ ጋር በተናጥል ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  • ተጫራቾች የሚያቀርቡት ሰነድ ስማቸውን ፊርማቸውንና አድራሻቸውን ማስፈር የድርጅቱን ማህተም መምታት ያለባቸው ሲሆን በጨረታው ሰነድ ላይ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም።
  • ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን እና ሌሎች ተፈላጊ መረጃዎች በአንድ ኢንቨሎፕ በማሸግ ማለትም 1 ኦርጅናል 1 ኮፒ በመለያየት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ የደ/ኢት/ክ/መ ፕላንና ልማት ቢሮ እንደኛ ፎቅ ግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር በመቅረብ ዘወትር በሥራ ሰዓት ላይ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ማስገባት ይጠበቅበታል።
  • ይህ ጨረታ አየር ላይ የሚቆየው ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 05 ቀናት ሲሆን ጨረታው በ 6ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4፡30 ሰዓት ላይ የደ/ኢት/ክ/መ ፕላንና ልማት ቢሮ ተጫራቾች ወኪሎቻቸው በተገኙበት በይፋ ይከፈታል።
  • ተጫራቾች ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታው ከመከፈት አይታገድም።
  • ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የሕዝብ በዓል ላይ ከዋለ ጨረታው የሚከፈተው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት እና ቦታ ይሆናል።
  • ይህ የጨረታ ዋጋ ለ45 የሥራ ቀናት ጸንቶ የሚቆይ ይሆናል።
  • ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል የደ ኢት/ክ/መ ፕላንና ልማት ቢሮ ግ/ፋ/ን/አስ/ዳይፊክቶሬት ቀርበው መግዛት ይችላሉ።
  • መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡ 046 180 2396/ 046 180 4910
የደ/ኢት/ክ/መ ፕላንና ልማት ቢሮ


Tender details

  • Deadline: 2026-05-19
  • Bid closing time: 12:00
  • Bid closing (note): ይህ ጨረታ አየር ላይ የሚቆየው ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ6ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-05-19 12:00
  • Bid opening (note): ይህ ጨረታ አየር ላይ የሚቆየው ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ6ኛው ቀን በ4፡30 ሰዓት
  • Region: South Ethiopia Regional State
  • Publishing entity: የደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መ ፕላንና ልማት ቢሮ
  • Bid bond: 10,000.00 ብር
  • Bid document price: 200.00 ብር
  • Published: May 14, 2026
  • Posted at: 2026-05-14T07:28:52.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders