ጸደይ ባንክ አ.ማ. ስፋቱ 306 ካ.ሜ. የሆነ የመኖሪያ ቤትና ቦታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Description
የሀራጅ ጨረታ ማስታወቂያ
ጸደይ ባንክ አ.ማ ለአቶ ሃብታሙ በላቸው ለሰጠው ብድር በዋስትና ያስያዘውን በአምበር ከተማ በካርታ ቁጥር 1122 የተመዘገበ በአዋሳኝ በምስራቅ አለማየሁ ዳምጤ ተስፋ፣ በምዕራብ ክፍት ቦታ፣ በሰሜን መንገድ፣ በደቡብ አማኑ ተመስጌን የሚያዋስነው ስፋቱ 306 ካ/ሜ የሆነ የመኖሪያ ቤትና ቦታ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል። በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል።
1. ተጫራቾች የቤቱን የጨረታ መነሻ ዋጋ 1/4ኛ በጥሬ ገንዘብ ወይም ሲፒኦ በጸደይ ባንክ ስም ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
2. የቤቱ ጨረታ መነሻ ዋጋው ብር 2,211,998.85 /ሁለት ሚሊየን ሁለት መቶ አስራ አንድ ሽ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ስምንት ብር ከሰማንያ አምስት ሳንቲም/ ነው።
3. በጨረታ የሚሳተፈው በህግ ሰውነት ያገኘ ድርጅት ከሆነ የድርጅቱን የጸደቀ የመመስረቻ ጽሁፍ እና መተዳደሪያ ደንብ፣ ህጋዊ ሰውነት ያገኘበት የምዝገባ የምስክር ወረቀት እንዲሁም ህጋዊ ውክልና ማቅረብ አለበት።
4. የጨረታ አሸናፊው አሸናፊነቱ የሚረጋገጠው የጨረታው ውጤት በሚመለከተው አካል ጸድቆ በባንኩ ደብዳቤ ሲሰጠው ይሆናል።
5. የጨረታ አሸናፊው ያሸነፈበትን ቀሪውን ገንዘብ በ15 ቀን ውስጥ ለባንኩ በመክፈል ያሸነፈበትን ንብረት መረከብ ይኖርበታል። በዚህ ቀን ውስጥ ካልከፈለ ግን ጨረታው ተሰርዞ ያስያዘው 1/4ኛ ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል።
6. በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል።
7. የጨረታ አሸናፊው ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያየዙ ማናቸውንም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች፣ ግብር፣ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ፣ እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውም ወጭዎችን ይከፍላሉ። ውዝፍ የሊዝ ክፍያ ካለ ባንኩ የሚከፍል ሲሆን ለቀሪው የሊዝ ክፍያ ገዡ ከሚመለከተው የመንግስት አካል ጋር ይዋዋላል።
8. ተጫራቾች ቤቱን በባንኩ አማካኝነት መጎብኘት ወይም ማየት ይችላሉ።
9. ጨረታው የሚካሄደው አምበር ከተማ ቀበሌ 01 ለጨረታ በወጣው ንብረት ውስጥ ነው።
10. ጨረታው የሚካሄደው ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት እስከ 6፡30 ሰዓት ይሆናል።
11. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ _ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
12. ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 12 43 68 68/ 09 21 66 71 15 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።
Tender details
- Deadline: 2026-06-23
- Bid closing time: 12:30
- Bid opening: 2026-06-23 12:30
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Tsedey Bank S.C.
- Buyer address: Legahar Orda Building, 8th Floor room No-804
- Bid bond: 25%
- Published: May 17, 2026
- Posted at: 2026-05-18T12:49:11.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.