የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቁጥር 33/2018 በ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት ላይ የሚውሉ የኤሌክትሮኒክስ የዕቃዎች እና የጽህፈት መሳሪያዎች ግዥ በሀገር ውስጥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቁጥር 33/2018 በ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት ላይ የሚውሉ የኤሌክትሮኒክስ የዕቃዎች እና የጽህፈት መሳሪያዎች ግዥ በሀገር ውስጥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

በዚሁ መሰረት፦

1. በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ እና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ።

2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።

3. ተጫራቾች ጨረታውን በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል በሚገኘው በፌዴሬሽኑ 2 ፎቅ ቁጥር 6 በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።

4. ተጫራቾች የመጫረቻ ስነዶቻቸውን ዋናውንና ኮፒውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

5. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስረኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ዕለት 4፡30 ሰዓት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 (መሰብሰቢያ አዳራሽ) ይከፈታል

6. ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዕቃዎች ለእያንዳንዱ ዕቃ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል።

7. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መስሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።

8. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

9. ተጫራቾች - የሚጫረቱት በዘርፉ የተሰማሩ መሆን አለባቸው።

አድራሻ፡- ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 ለበለጠ መረጃ፡- 011647-97-94/ 01164795-78 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

ፋክስ 0116 45_08

79 ፖ.ሳ.ቁ 13336

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን


Tender details

  • Deadline: 2026-05-28
  • Bid closing time: 12:00
  • Bid closing (note): ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ በአስረኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-05-28 12:00
  • Bid opening (note): ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ በአስረኛው ቀን በ4፡30 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Ethiopian Athletics Federation
  • Buyer address: ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕንጻ 2 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6
  • Bid bond: 50,000.00 ብር
  • Bid document price: 200.00 ብር
  • Published: May 17, 2026
  • Posted at: 2026-05-18T12:53:42.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders