የዳንግላ ከተማ አስተዳደር መሬት ጽ/ቤት ለመኖሪያ እና ለድርጅት አገልግሎት የተዘጋጁ ቦታዎችን 3ኛ ዙር በግልጽ ጨረታ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል

Description

የመሬት ሊዝ ጨረታ ማስታወቂያ

የዳንግላ ከተማ አስተዳደር መሬት ጽ/ቤት የመሬት ማስተላለፍ ቡድን የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነግገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 መሠረት ለመኖሪያ እና ለድርጅት አገልግሎት የተዘጋጁ ቦታዎችን 3ኛ ዙር በግልጽ ጨረታ ለተጫራቾች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም፡-

  1.  ጨረታው ከግንቦት 10/2018 ዓ/ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ይቆያል፡፡
  2. የቦታውን ዝርዝር መረጃ እና ለጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ዳንግላ ከተማ አስተዳደር መሬት ጽ/ቤት የመሬት ማስተላለፍ ቡድን ቢሮ ቁጥር 07 ድረስ በመምጣት ዘወትር በስራ ስዓት ሰነድ መግዛት እና መወዳደር ይችላሉ፡፡
  3. የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ እና መሸጫ ጊዜ ግንቦት 10/2018 ዓ/ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡00 ይሆናል፡፡
  4. ጨረታው የሚዘጋው 10 የስራ ቀናት ተቆጥረው በ10ኛው ቀን 11፡00 ሁሉም የጨረታ አስፈፃሚ ቡድን አባላት እና አግባብ ያለው አካል የሚሰይማቸውን ታዛቢዎች በተገኙበት ይሆናል፡፡
  5. ቦታውን መጎብኘት ለሚፈልጉ ተጫራች በተቋሙ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በሚገለፀው መርሃ ግብር መሠረት የምናስጎበኝ ይሆናል፡፡
  6. ጨረታው የሚከፈተው ጨረታው ዝግ ከተደረገበት ቀን በኋላ ባለው የመጀመሪያ የስራ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአገው ምድር አዳራሽ ይሆናል፡፡
  7. መ/ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  8. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ በዳንግላ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ቦታዎች በሚለጠፋ ማስታወቂያዎች እና ቢሮ ቁጥር 06 ወይም በስልክ ቁጥር 058 221 07 72 /058 221 19 83 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የዳንግላ ከተማ አስተዳደር መሬት ጽ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-05-28
  • Bid closing time: 17:00
  • Bid closing (note): ጨረታው የሚዘጋው 10 የስራ ቀናት ተቆጥረው በ10ኛው ቀን 11፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-05-29 10:00
  • Bid opening (note): ጨረታው የሚከፈተው ጨረታው ዝግ ከተደረገበት ቀን በኋላ ባለው የመጀመሪያ የስራ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት
  • Region: Amhara
  • Publishing entity: Dangela City Administration Urban Development & Land Development Bureau
  • Bid document price: 300.00 ብር
  • Published: May 18, 2026
  • Posted at: 2026-05-21T09:05:17.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders