ወጋገን ባንክ አ.ማ. የኢንዱስትሪ ህንጻ (G+3) እና ተሽከርካሪ በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል

Description

ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ

ቁጥር፡ ወጋገን 026 /2018

ወጋገን ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011፤ 97/90 እና 216/92 መሰረት ከዚህ በታች የቀረቡትን የመያዣ ንብረቶች በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

የማይንቀሳቀስ ንብረት የሀራጅ ጨረታ ዝርዝር

ተ.ቁ

የተበዳሪው ስም

ንብረት አስያዥ

አበዳሪው ቅርንጫፍ

የንብረቱ አድራሻ

የቦታው ስፋት

 

የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ ቁጥር

የንብረቱ ዓይነት/ የይዞታው አገልግሎት

 

የጨረታ መነሻ ዋጋ

ጨረታው የሚከናወንበት ቀን

 

ከተማ/ክልል

 

ክ/ከተማ ከተማ/ዞን

ወረዳ/ቀበሌ

1

ሮቤል ወ/ማርያም

ሮቤል ሙሉ

ውኃልማት

ትግራይ

መቐለ

 

ሰሜን

 

5,000 ካ/ሜትር

423/01/14452

 

የኢንዱስትሪ ህንጻ (G+3)

 

37,236,160.29

 

ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጧቱ 3፡00 – 6፡00 ሰዓት

 የተሽከርካሪ የሀራጅ ጨረታ ዝርዝር

ተ.ቁ

የተበዳሪው ስም

ንብረት አስያዥ

አበዳሪ ቅርንጫፍ

የተሽከርካሪ ዓይነት

የሰሌዳ ቁጥር

የሻንሲ ቁጥር

የሞተር ቁጥር

ዘመን

 

የነዳጅ አይነት

የጨረታ መነሻ ዋጋ ብር

ጨረታው የሚከናወንበት ቀን

ቀን

 ሰዓት

1

ኤን ኤይ ኤች ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/ግ/ማህበር

ተበዳሪው ድርጅት

 

ሰባራ ባቡር

 

ድርብ ተግባር (ፒክአፕ)

አአ-03-B33007

 

AHTKB8CD302980881

 

2GD-4971804

 

2021

ናፍጣ

 

3,800,000.00

 

ሰኔ 01 ቀን 2018 ዓ.ም. 

ከጧቱ 3፡00-6፡00 ሰዓት ድረስ

 ማሳሰቢያ

  1. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የጨረታ መነሻ ዋጋ ¼  (አንድ አራተኛ) በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ (C.P.O) በወጋገን ባንክ አ.ማ ስም በማሰራት በጨረታው ዕለት በመቅረብና በመመዝገብ በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ።
  2. የጨረታ አሸናፊ ከባንኩ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ከተሰጠው ቀን ጀምሮ ቀሪውን ገንዘብ በ15 /አስራ አምስት ቀናት ውስጥ አጠናቆ መክፈል ይኖርበታል. ባይከፍል ግን የሐራጁ ውጤት ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፤ ላላሸነፉት ተጫራቾች ግን ያስያዙት ሲፒኦ ወዲያዉኑ ይመለስላቸዋል።
  3. ጨረታውን ላሸነፈ፣ የባንኩን የብድር ፖሊሲ፣ መመሪያ እና ቅድመ ሁኔታ ለሚያሟላ እንዲሁም ተጨማሪ የመያዣ ንብረት ለሚያቀርብ ተጫራች፣ ባንኩ በብድር መመሪያ መሰረት ብድር ሊያመቻች ይችላል።
  4. የተጫራቾች የምዝገባ ሰዓት ከጧቱ 3፡00 - 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ሊሆን ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ለንብረቱ የሚመደበው የጥሪ ሰዓት 30 ደቂቃ ብቻ ነው። ሆኖም የጨረታው መጠናቀቂያ ሰዓት ድረስ አሽናፊው ካልተለየ አሸናፊ እስኪለይ ድረስ ጨረታው ይቀጥላል።
  5. በጨረታው የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ጨረታውን ካካሄደው ከባንኩ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ሲደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል።
  6. ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል።
  7. ጨረታው የሚካሄደው በመጀመሪያው ሰንጠረዥ ላይ የተጠቀሰው መቐለ ከተማ በሚገኘው በወጋገን ባንክ ቺፍ ሰሜን ሪጅናል ጽ/ቤት ሲሆን በሁለተኛው ሰንጠረዥ ላይ የተገለጸው በባንኩ ዋና መስርያ ቤት ህንጻ 13ኛ ወለል ላይ በሚገኘው የመሰብሰብያ አዳራሽ ይሆናል።
  8. ለሀራጅ ጨረታ የቀረበውን ንብረት ለመጎብኘት የሚፈልግ ተጫራች የጨረታው ቀን ከመድረሱ በፊት ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በማስያዝ መጎብኘት ይችላል።
  9. ተበዳሪው ንብረት አስያዥ ወይም ሁለቱም በጨረታው ቀን እና ሰዓት በቦታው ላይ መገኘት ይችላሉ። ነገር ግን ተበዳሪው ንብረት አስያዙ/ በጨረታ ቀን እና ሰዓት በቦታው ባይገኝ ጨረታው በሌለበት ይካሄዳል። ከዚህ በተጨማሪ ጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች ወይም የተጫራቾች ህጋዊ ተወካዮች ብቻ ናቸው።
  10. ማንኛውንም ለመንግስት ሊከፈል የሚገባውን ክፍያ ተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ የጨረታው አሸናፊ የሚከፍል ይሆናል።
  11. ለበለጠ ማብራሪያ ወይም የጉብኝት ቀጠሮ ለማመቻቸት ወጋገን ባንክ አ.ማ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት 011-558-1837 የባንኩ ቺፍ ሰሜን ሪጅናል ጽ/ቤት፡ 034-241-5185/ 034-241-5186 መደወል ይችላሉ።
  12. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም።

ወጋገን ባንክ አ.ማ


Tender details

  • Deadline: 2026-06-23
  • Bid closing time: 12:00
  • Bid closing (note): የሐራጁ መዝጊያ ቀንና ሰዓት የተለያየ ነው
  • Bid opening: 2026-06-23 12:00
  • Bid opening (note): የሐራጁ መክፈቻ ቀንና ሰዓት የተለያየ ነው
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Wegagen Bank S.C.
  • Bid bond: 25%
  • Published: May 24, 2026
  • Posted at: 2026-05-25T10:37:06.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders