ቡና ባንክ አ.ማ. ንብረቶች በግልጽ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Description
የሐራጅ ማስታወቂያ
ቁጥር፤ ቡባ/ሕአዳ/ሐራጅ/036/2018
ቡና ባንክ አ.ማ. በአዋጅ ቁ. 97/1990 (እንደተሻሻለው) በተሰጠው ስልጣን መሠረት ቀጥሎ የቀረቡትን ንብረቶች በግልጽ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ. |
የተበዳሪ ስም |
የንብረት አስያዥ ስም |
አበዳሪ ቅርንጫፍ |
ለጨረታ የቀረበው ንብረትና የቦታ ስፋት |
የጨረታ መነሻ ዋጋ በብር |
ጨረታው የሚከናወንበት |
ጨረታው የወጣው |
||||
|
ለጨረታ የቀረበው ንብረት |
ከተማ/ክ/ከተማ/ ቀበሌ ወረዳ/ የቤት ቁጥር |
የካርታ ቁጥር |
የቦታ ስፋት |
ቀን |
ሰዓት |
||||||
|
1 |
አቶ አለማየሁ ፊጤ በየነ |
ተበዳሪ |
ጎፋ |
የመኖሪያ ቤት |
በኦሮሚያብ/ክ/መንግስት፤በሸገር ከተማ አስተዳደር የገፈርሳ ጉጄ ክ/ከተማ ፤ ኮሎቦ ከተማ ፤ቼሼር አካባቢ |
OR00012360703018 |
200 ካ.ሜ |
3,805,338.48 |
ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም |
8፡00-9፡00 |
ለመጀመሪያ ጊዜ |
|
2 |
ራማ ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/የግ/ማኅበር |
ተበዳሪ |
ሾላ ገበያ |
የሪል እስቴት ግንባታ (ያልተጠናቀቀ) |
በኦሮሚያ ብ/ክ/መ፣ ቢሾፍቱ ከተማ፣ ቀበሌ 05፣ |
24/139 |
77,760 ካ/ሜ |
125,183,980.53 |
ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም |
4፡00-5፡00 |
ለመጀመሪያ ጊዜ |
|
3
|
አቶ ሮቤል አለማየሁ አሰፋ
|
ተበዳሪ
|
ዓብይ
|
አፓርትመንት መኖሪያ ቤት |
ልደታ ክ/ከተማ ተግባረእድ አልሳም ሪልስቴት 16ኛ ፎቅ የቤ/ቁጥር A-16-03 |
AA000030901044 |
የቤቱ ስፋት 128.251 ካ.ሜ የጋራ መገልገያ ስፋት በፕሮፖርሽን 54.505 ካ.ሜ በድምሩ 182.756 ካ.ሜ |
21,931,200.00 |
ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም |
5፡00-6፡00 |
ለሁለተኛ ጊዜ |
የሐራጅ ደንቦች፣
- ተጫራቾች የሐራጁን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ (1/4ኛ) በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በቡና ባንክ አ.ማ ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ።
- አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ አሸናፊ መሆኑ በደብዳቤ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ ባሉት በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ ተጠቃሎ መከፈል አለበት፡፡ ካልተከፈለ የተያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሰረዛል፡፡ በተጨማሪም ንብረቱ ድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃሉ፡፡ ላላሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ በዕለቱ ይመለስላቸዋል።
- በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ ተበዳሪ እና ንብረት አስያዥ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ብቻ ናቸው፡፡ ተበዳሪ እና ወኪሎቻቸው ባይገኙም ሐራጁ በሌሉበት ይካሄዳል።
- የተጫራቾች ምዝገባ ከእያንዳንዱ የንብረት ሐራጅ መዝጊያ ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል፡፡ በሐራጁ የመጨረሻ ሰላሳ ደቂቃዎች የተጫራች ምዝገባ አይካሄድም።
- የሐራጁ አሸናፊ /ገዢ/ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውንም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን፤ ግብር በዋጋው ላይ የሚታሰብ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ (15%) ካለ ከስም ማዛወሪያ ክፍያ ጋር የተገናኙና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ታክስ እና ግብሮች ገዥው /አሸናፊው/ ይከፍላል።
- በሐራጁ የተዘረዘሩትን ንብረቶች ለማየት ከአበዳሪ ቅርንጫፉ ጋር በመነጋገር ፕሮግራም አስይዞ መጎብኘት ይቻላል።
- ተጫራቹ የጨረታው አሸናፊ ነው የሚባለው አሸናፊነቱን የሚገልፅ ደብዳቤ በጽሑፍ ሲደርሰው ብቻ ነው።
- ጨረታው በቡና ባንክ አ.ማ ዋናው መስሪያ ቤት ቦሌ ክፍለ ከተማ፤ ከወሎ ሰፈር አደባባይ ወደ ቦሌ ሲሄዱ ሩዋንዳ መታጠፊያ ሳይደርሱ በሚገኘው የባንኩ ሕንፃ 9ኛ ፎቅ በሚገኘው አዳራሽ ውስጥ የሚካሄድ ይሆናል።
- ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ ፣ ሕግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ስ.ቁ 011-1-58-08-63/011-1-26-36-09 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
Tender details
- Deadline: 2026-06-23
- Bid closing time: 15:00
- Bid closing (note): የጨረታ መዝጊያ ሰአት የተለያየ ነው
- Bid opening: 2026-06-23 15:00
- Bid opening (note): የጨረታ መክፈቻ ሰአት የተለያየ ነው
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Bunna Bank S.C.
- Bid bond: 25%
- Published: May 24, 2026
- Posted at: 2026-05-25T13:04:19.000Z
- Buyer website: https://bunnabanksc.com/
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.