በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራርና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን ሀገራዊ ስትራተጂክ ከምችት አቅም ለማሳደግ ለምግብነት የሚውል ጥሬ በቆሎ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
Description
ለምግብነት የሚውል ጥሬ በቆሎ ግዥ 468/18
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራርና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን ሀገራዊ ስትራተጂክ ከምችት አቅም ለማሳደግ ለምግብነት የሚውል ጥሬ በቆሎ ግዥ በግልጽ ጨረታ ከዚህ በታች በሰንጠረዥ በተዘረዘረው መሰረት በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
|
ተ/ቁ |
የዕቃው አይነት |
መለኪያ |
ብዛት |
የጨረታ ማስከበሪያ |
የሚታሸግበት ሰዓት |
|
1 |
ለምግብነት የሚውል ጥሬ በቆሎ ግዥ |
በኩንታል |
30,000 |
100,000 |
በ16ኛው ቀን በ4፡00 ታሽጎ በዕለቱ 4፡10 ይከፈታል |
በንግድ ስራ ዘርፉ የታደሰ ፍቃድ፣ የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፣ በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸውና የቫት መዝጋቢነት ማስረጃዎች ያላቸውና የሚያቀርቡ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ለ60 ቀናት የፀና መሆን ይኖርበታል።
- በተጫራቾች የሚቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ያስያዙበትን ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች በቢሮ የተዘጋጀውን መደበኛ የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባለው ተከታታይ እስከ 15ኛ ቀን 11፡30 ድረስ የማይመለስ ብር ለእያንዳንዱ ሎት 300(ሶስት መቶ ብር) በመክፈል በዲላ ከተማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ መምህራን ኮሌጅ ግቢ ከሚገኘው የግብርና ቢሮ ግዥ/ንብ/አስ/ዳይሬከቶሬት ክፍል መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ በመሙላት ይህ የጨረታ የቴክኒካልና ፋይናንሻል አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ የመጫረቻ ሰነዶች በአንድነት ፖስታ በማዘጋጀት በ16ኛው በቢሮ ግዥ/ንብ/አስ/ዳይሬከቶሬት ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይቻላል። እንዲሁም ተጫራቾች(ተወካዮቻቸው) በተገኙበት በቢሮው የግዥ/ንብ/አስ/ዳይሬከቶሬት ከፍል ይከፈታል።
- ቢሮው በቀረበው ጨረታ ላይ ካሸናፊው ድርጅት ጋር ውል ከመፈራረሙ በፊት የግዥውን 20% ፐርሰንት መቀነስ ወይም መጨመር ይችላል።
- ከ200,000 ሺህ በላይ ለሆኑት ግዥዎች ተጫራቾች ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው።
- የጨረታው ሳጥን መክፈቻ በ16ኛው ቀን የመንግስት የስራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በቀጣይ ባለው የስራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓትና ቦታ የሚከፈት ይሆናል።
- ሁለት ተወዳዳሪዎች ያቀረቡት ዋጋቸው እኩል በሚሆንበት ወቅት በእጣ የሚለይ ይሆናል።
- ቢሮው ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ:- 046-131-0134 ይጠቀሙ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ
Tender details
- Deadline: 2026-06-25
- Publishing entity: Southern Ethiopia Bureau of Agriculture
- Bid bond: 100,000.00 ብር
- Bid document price: 300.00 ብር ለእያንዳንዱ ሎት
- Published: Jun 10, 2026
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.