ፀደይ ባንክ /አ.ማ/ ደ/ማርቆስ ዲስትሪክት ስፋቱ 150 ካ.ሜ የሆነ የመኖሪያ ቤትና ቦታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Description
ፀደይ ባንክ/አ.ማ/ ደ/ማርቆስ ዲስትሪክት
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የሀራጅ ጨረታ ማስታወቂያ
ጸደይ ባንክ አ.ማ ለወ/ሮ መሰረት ተሻገር ለሰጠው ብድር በዋስትና ያስያዘውን በደ/ማርቆስ ከተማ በካርታ ቁጥር K/አብ-01007 የተመዘገበ በአዋሳኝ በምስራቅ መንገድ፣ በምዕራብ ያሳብ አያሌው፣ በሰሜን ዳዊት አያሌው፣ በደቡብ ሽበሽ ገላየ የሚያዋስነው ስፋቱ 150 ካ/ሜ የሆነ የመኖሪያ ቤትና ቦታ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በድጋሚ ለ2ኛ ጊዜ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል:: በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የቤቱን የጨረታ መነሻ ዋጋ 1/4ኛ በጥሬ ገንዘብ ወይም ሲፒኦ በጸደይ ባንክ ስም ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
- የቤቱ ጨረታ መነሻ ዋጋው ብር 3,452,861,48 /ሶስት ሚሊዮን አራት መቶ አምሳ ሁለት ሺ ስምንት መቶ ስልሳ አንድ ከአርባ ስምንት ሳንቲም/ ነው።
- በጨረታ የሚሳተፈው በህግ ሰውነት ያገኘ ድርጅት ከሆነ የድርጅቱን የጸደቀ የመመስረቻ ጽሁፍ እና መተዳደሪያ ደንብ፣ ህጋዊ ሰውነት ያገኘበት የምዝገባ የምስክር ወረቀት እንዲሁም ህጋዊ ውክልና ማቅረብ አለበት።
- የጨረታ አሸናፊው አሸናፊነቱ የሚረጋገጠው የጨረታው ውጤት በሚመለከተው አካል ጸድቆ በባንኩ ደብዳቤ ሲሰጠው ይሆናል።
- የጨረታ አሸናፊው ያሸነፈበትን ቀሪውን ገንዘብ በ15 ቀን ውስጥ ለባንኩ በመክፈል ያሸነፈበትን ንብረት መረከብ ይኖርበታል:: በዚህ ቀን ውስጥ ካልከፈለ ግን ጨረታው ተሰርዞ ያስያዘው 1/4ኛ ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል።
- በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል።
- የጨረታ አሸናፊው ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያየዙ ማናቸውንም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች፣ ግብር፣ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ፣ እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውም ወጭዎችን ይከፍላሉ:: ውዝፍ የሊዝ ክፍያ ካለ ባንኩ የሚከፍል ሲሆን ለቀሪው የሊዝ ክፍያ ገዥው ከሚመለከተው የመንግስት አካል ጋር ይዋዋላል።
- ተጫራቾች ቤቱን በባንኩ አማካኝነት መጎብኘት ወይም ማየት ይችላሉ።
- ጨረታው የሚካሄደው ደ/ማርቆስ ከተማ ቀበሌ 13 ለጨረታ በወጣው ንብረት ውስጥ ነው።
- ጨረታው የሚካሄደው ሃምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት እስከ 6፡30 ሰዓት ይሆናል።
- ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0912436868 / 0921667115 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።
Tender details
- Deadline: 2026-07-27
- Bid closing time: 12:30
- Bid opening: 2026-07-27 12:30
- Region: Amhara
- Publishing entity: Tsedey Bank S.C. Debre Markos District
- Bid bond: 25%
- Published: Jun 21, 2026
- Posted at: 2026-06-22T09:59:46.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.