በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የባህዳር ከተማ ጣና ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤት 500 ካሬ ሜትር ቤት መሸጥ ይፈልጋል

Description

 

የሃራጅ ጨረታ ማስታወቂያ

አፈ/ከሳሽ-ህብረት ባንክ

አፈ/ተከሳሽ------- ታወር አልሙኒየም ኢንጅነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክስ ክርክር ጉዳይ በባህርዳር ከተማ ጣና ክፍለ ከተማ በኢንዱስትሪ ፖርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ስር በአፈ/ተከሳሽ ስም ተመዝገቦ የሚገኘውን በአዋሳኝ በምስራቅ መኮነንነ አሳየ፣ በምዕራብ መንገድ፣ በሰሜን ዋግነር ትሬዲንግ፤ በደቡብ መንገድ መካከል ተዋስኖ የሚገኘውን 500 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ቤትና ቦታ በመነሻ ዋጋው ዐ /ዜሮ/ ሆኖ ከፀደይ ባንክ ብር 4,428,483.61 አራት ሚሊዮን አራት መቶ ሃያ ስምንት ሺህ አራት መቶ ሰማኒያ ሶስት ብር ከስልሳ አንድ ሳንቲም እዳ ያለበት መሆኑን አውቃችሁ 18/11/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 6፡00 ሰዓት ድረስ በግልፅ ጨረታ ስለሚሸጥ ማንኛውም ተጫራች ቤቱ በሚገኝበት በባ/ዳር ከተማ ጣና ክ/ከተማ በመገኘት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ መጫረት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፣ በእለቱ ጨረታውን ያሸነፈ ያሸነፈበትን 1/4ኛውን በሞ/85 ጨረታው እንደተጠናቀቀ ወዲያውኑ እንድታስይዙ ፍ/ቤቱ አዟል።

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የባህዳር ከተማ

ጣና ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-07-25
  • Bid closing time: 12:00
  • Bid opening: 2026-07-25 12:00
  • Region: Amhara
  • Publishing entity: ባህዳር ከተማ ጣና ክፍለ ከተማ ፍርድ ቤት
  • Published: Jun 25, 2026
  • Posted at: 2026-06-25T07:24:37.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders