በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ፅ/ቤት የተለያዩ የፅህፈት መሳሪያ እቃዎች፣ የተለያዩ አላቂ የፅዳት እቃዎች፣ የተለያዩ ቀለሞች እና የተሽከርካሪ ጎማ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Description
ብሄራዊ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር-001/2019
በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ፅ/ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ለከተማው ሴከተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ እቃዎችን በጥቅል ግዥ ለመፈፀም በብሄራዊ ግልፅ ጨረታ በዘርፉ ህጋዊ ፍቃድ ባላቸው አቅራቢዎች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- ሎት 1 የተለያዩ የፅህፈት መሳሪያ እቃዎች፣
- ሎት-2 የተለያዩ አላቂ የፅዳት እቃዎች፣
- ሎት-3 የተለያዩ ቀለሞች፣
- ሎት 4 የተሽከርካሪ ጎማ
በዚህም መሰረት፡- ከዚህ በታች የተገለጹትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ድርጅቶች በጨረታው እንዲሳተፉ ተጋብዘዋል።
- ተጫራቾች በጨረታው ለመካፈል ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆኑን የሚያሳይ መረጃ (የታክስ ክሊራንስ) ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ተመዝጋቢ የሆኑና ስለዚህ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል። እንዲሁም የንግድ መለያ ቁጥር/TIN NUMBER/ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች (egp) በኦን ላየን የተመዘገባችሁ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባችኋል።
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የጨረታ ማስከበሪያ በወልቂጤ ከተማ ፋይናንስ ፅ/ቤት ስም ከታወቀ ባንክ የተረጋገጠ ቼክ፤ CPO ለእያንዳንዱ ጨረታ ወይም ሎት 50,000(ሃምሳ ሺ ብር) በማሰራት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበት የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500/አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት ከወ/ጤ ከተማ ፋይናንስ ፅ/ቤት ግ/ን/አስ/ዋና/ስራ ሂደት ክፍል ቀርቦ መውሰድ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
- ተወዳዳሪዎች የጨረታውን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15/ለአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት አየር ላይ የሚውሉ ሲሆን በ16ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 የጨረታው ሳጥን ታሽጎ በዚሁ ቀን 8፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናውንና ሁለት ኮፒውን በተናጠል ለይቶ በማሸግ በአንድ እናት ፖስታ በማድረግ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ አሽገው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- መ/ቤቱ የጨረታ አሸናፊ ተወዳዳሪ የሚለየው ተወዳዳሪዎች ለእያንዳንዱ ነጠላ እቃ ባቀረቡት ዋጋ መሰረት የቀረበ አነስተኛ ዋጋ ወይም በጥቅል ሎት በማየት የተሻለውን የጨረታ አሸናፊ የመለየት ስራ ሊሰራ ይችላል።
ማሳሰቢያ ፅ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
- በጨረታው መክፈቻ ቀንና ሰአት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙ ጨረታው ከመክፈት አያስተጓጉልም።
- መ/ቤቱ ከሸጠው ሰነድ ውጪ በሌላ ሰነድ ሞልቶ መወዳደር አይቻልም።
- የጨረታ ማስታወቂያውንና የጨረታ ሰነዱ የሚጠይቀውን ዝቅተኛ መስፈርት የማያሟሉ ተጫራቾች ወይም አቅራቢዎች ከጨረታው ውጪ ይደረጋሉ።
- የጨረታውን መክፈቻ ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም ብሄራዊ የህዝብ በዓል ከሆነ ቀጣይ ወዳለው የስራ ቀን ይተላለፋል።
ለበለጠ መረጃ አድራሻ፡- በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ፅ/ቤት ከብሩክ ህንፃ ፊት ለፊት ቴሌ አጠገብ ከተሰራው አዲሱ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ህንፃ ውስጥ 1ኛ ፎቅ ወደ ቀኝ ሲታጠፉ የወልቂጤ ከተማ ፋይናንስ ፅ/ቤት በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0113301548/0911921780/ደውለው ማነጋገር ይችላሉ።
የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ፅ/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-07-30
- Publishing entity: Welkite City Administration Finance and Economic Development Bureau
- Bid bond: 50,000.00 ብር ለእያንዳንዱ
- Bid document price: 500.00 ብር
- Published: Jul 15, 2026
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.