በማ/ኢ/ክ/መ/በጉራጌ ዞን ቸሀ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት እስቴሽነሪ፣ የሞተር ጎማ እና የጽዳት እቃዎች በጨረታ አወዳደሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ/ዐ1/

በማ/ኢ/ክ/መ/በጉራጌ ዞን ቸሀ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ለሴክተር መ/ቤት አገልግሎት የሚውል  

  • lot one እስቴሽነሪ፤
  • lot two የሞተር ጎማ፣
  • lot three የጽዳት እቃዎች በጨረታ አወዳደሮ መግዛት ይፈልጋል።

 ስለሆነም፤

  1. በየንግድ ዘርፉ የተሰማራችሁ ተወዳዳሪዎች የዘመኑ ግብር የከፈላችሁ የታደሰ ንግድ ፈቃድና የምዝገባ ምስከር ወረቀት የቫት ተመዝጋቢ መሆናችሁ ማስረጃ ማቅረብ የምትችሉና ከዚህ በፊት በጨረታ ያልታገዳችሁ፤
  2. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት የጨረታውን ሰነድ ቸሀ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 7 በመቅረብ የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር በመክፈል መግዛት የምትችሉ መሆኑ፤
  3. ተጫራቾች የጨረታ ዶክመንታችሁ ላይ በእያንዳንዱ ገጽ ላይ የድርጅቱ ማህተምና ፊርማ በማድረግ ከላይ በተራ ቁጥር 1 ላይ የተዘረዘሩ ማስረጃዎች ኦርጅናል ሰነድና ኮፒ በተለያዩ በታሸጉ ፖስታዎች በማድረግ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት አላባችሁ።
  4. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ከ/15/ አስራ አምስት/ የሥራ ቀናት አየር ላይ ይውላል፤ እስከዚያ ድረስ የጨረታ ዶክመንታችሁን ማስገባት ይኖርባችኋል። ጨረታው የሚያበቃው የመጨረሻው ቀን ከቀኑ 8፡00 /ስምንት ሰዓት ሲሆን የሚከፈተው በዚሁ ቀን ከቀኑ 8፡30 /ስምንት ተኩል/ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሲሆን ባይገኙበት ጨረታው ለመክፈት የሚያግድ የሌለ መሆኑን እየገለጽን በዓል ቅዳሜና እሁድ ከሆነ የሚቀጥለው የሥራ ቀን ይተላላፋል።
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ገንዘብ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ እስቴሸነሪ /40000/ አርባ ሺህ ብር፤ የሞተር ጎማ 15000 /አስር አምስት ሺህ ብር/፣ የጽዳት እቃ 25000 /ሃያ አምስት ሺህ ብር/ማስያዝ ይኖርባችኋል።
  6. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ማሳሰበያ : የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት በኦላይን የተመዘገባችሁ ብቻ በጨረታው የምትሳትፉ ሲሆን ከዚህ ውጭ የሚመጣ ተጫራች ከጨረታ ውጭ ይሆናል፡፡

ለበለጠ መረጃ 011 331 0812/ 011 331 0254

በማ/ኢ/ክ/በጉራጌ ዞን አስተዳደር የቸሃ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-08-01
  • Publishing entity: Guraghe Zone Cheha Woreda Finance Office
  • Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
  • Bid document price: 300.00 ብር
  • Published: Jul 16, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders