ኦሮሚያ ባንክ አ.ማ. መኖሪያ ቤት ባሉበት በግልጽ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል

Description

የሐራጅ ማስታወቂያ

ኦሮሚያ ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90እና 216/92 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ለሰጠው ብድር በዋሰትና የያዘዉን በሰንጠረዡ ላይ የተዘረዘሩትን ንብረቶች ባሉበት በግልጽ ሐራጅ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

ተ.ቁ

የተበዳሪው ስም

የንብረት አስያዥ ስም

ለጨረታ የቀረበው ንብረት ዓይነት

አበዳሪ ቅርንጫፍ

ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻና የቦታ ስፋት

የጨረታ መነሻ ዋጋ

 

የጨረታዉ ቀን፣ ሰዓት እና ጨረታው የሚካሄድበት ቦታ

ጨረታው የወጣው

 

ከተማ፣ // ወረዳ/ ቀበሌ

የባለቤትነት ማረጋገጫ ቁጥር

 

የቦታ ስፋት በካ./ ሄክ

1

አቶ አብደላ ሹኩሬ ራህመቶ

ተበዳሪው

መኖሪያ ቤት

ቡታጅራ  

ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስ/ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ሽርሼ ቀበሌ

SN013030403020

 

252.52 ካ.ሜ

 

4,605,974.19

 

14/12/2018 03:00-4:00 ሰዓት በኦሮሚያ ባንክ ውስጥ

 

ለመጀመሪያ ጊዜ

2

አፋን ኮፊጀነራል ትሬዲንግ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር

ወ/ሮ ሽታዬ አያሌው ወጋየው

የመኖሪያ ቤት G+2

 

ባቦ

ሸገር ከተማ፣ መልካ ኖኖ /ከተማ፣ ወረዳ ቤሮ፣ ዲያስፖራ ሰፈር ቦሪያድ /ቤት አካባቢ

Bur/2845/98

 

250

21,191,529.04

 

14/12/2018 . 03:00-4:00 በዋና  መስሪያ ቤት

 

 

ለመጀመሪያ ጊዜ

 

  1. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የጨረታውን መነሻ ዋጋ 25% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ/ሲ.ፒ.ኦ በኦሮሚያ ባንክ ስም አሰርተው ጨረታው በሚካሄድበት ዕለት ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል:: በጨረታው ከፍተኛ ዋጋ ላልሰጡ ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ወዲያዉኑ ይመለስላቸዋል።
  2. ተራ ቁጥር 2 ላይ የተጠቀሰው  ንብረት ጨረታው በሰንጠረዡ ላይ በተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት ቦሌ መንገድ ኦሎምፒያ አካባቢ ስምራን ሆቴል ጎን የኦሮሚያ ባንክ የህግ አገልግሎት የሚገኝበት ናትሩት ሀሙስ (ህንፃ) 9ኛ ፎቅ ላይ ተራ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሰው ንብረት የሚገኝ የጨረታ አዳራሽ ውስጥ ባለዕዳዎቹ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው እና ታዛቢዎች በተገኙበት ይካሄዳል:: ባለ ዕዳዎች እና ታዛቢዎች ባይገኙም ጨረታው  ይካሄዳል።
  3. የተጫራቾች ምዝገባ ከሐራጅ መዝግያ ሰዓት 5 ደቅቃ በፊት ይጠናቀቃል:: የጨረታ መጠናቀቂያ ሰዓት ድረስ ከፍተኛ ዋጋ የሰጠ ተጫራች ካልተለየ እስኪለይ ደረስ ጨረታው የሚቀጥል ይሆናል:: በጨረታ ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ከባንኩ ህግ አገልግሎት ሲደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል።
  4. ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች አሸናፊ መሆኑ በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ዋጋ በ15 ቀን ውስጥ ለባንኩ አጠቃሎ ገቢ ማድረግ ይኖርበታል:: በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ገቢ የማያደርግ የጨረታ አሸናፊ ያስያዘው ሲፒኦ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል:: በተጨማሪም ንብረቱ በድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚፈጠረው ልዩነት ይጠየቃል።
  5. በባንኩ ብድር ፖሊሲ መሰረት የሚፈለገውን ማስረጃ አሟልቶ  ለቀረበ የጨረታ አሸናፊ ባንኩ ብድር ሊያመቻች ይችላል።
  6. ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች ንብረቱን በማስተሳስር ሂደት ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች ግብር፣ የሊዝ ክፍያ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፤ የስም ማዘወሪያ እና ማናቸዉም  ከጨረታው ጋር በተገናኘ መንግስት የሚጠይቀው ክፍያ ይከፍላል:: ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል።
  7.  ውዝፍ የሊዝ ክፍያን በተመስከተ ከእዳ ተመላሽ ብር ካለ ከተመላሽ ብር ላይ የሚከፈል ሲሆን ተመላሽ ብር ከሌለ ግን የንብረቱ ጨረታ አሸናፊ ውዝፍ የሊዝ ክፍያን ሙሉ በሙሉ የሚከፍል ይሆናል።
  8. ተጫራቾች ለጨረታ የቀረቡትን ንብረቶች በስራ ሰዓት ፕሮግራም አስይዞ ለመጎብኘት ይችላሉ።
  9.  ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011 557 1372 እና +251923587384 ዋና መ/ቤት ሕግ አገልግሎት፣ ለተራ ቁ.1 በ 046-1151157/83 ኦሮሚያ ባንክ ቡታጅራ ቅርንጫፍ፣ ለተራ.ቁ 2 በ 0113/71-30-72/65/74 /0118-96-02-71 ኦሮሚያ ባንክ ባቦ ቅርንጫፍ ደውለው መጠየቅ ይቻላል።
  10. ባንኩ ጨረታውን በማንኛውም ጊዜ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ኦሮሚያ ባንክ አ.ማ.


Tender details

  • Deadline: 2026-08-20
  • Publishing entity: Oromia Bank S.C.
  • Bid bond: 25%
  • Published: Jul 19, 2026
  • Posted at: 2026-07-20T14:29:12+00:00

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders