Property and building foreclosure

የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የፍትሐብሔር ጉዳይ ችሎት የመኖሪያ ቤት መሸጥ ይፈልጋል

Description

ማስታወቂያ

በፍርድ ባለመብት ዶ/ር ሀይለልዑል ዘለቀ እና በፍርድ ባለዕዳ ወ/ሮ ራሔል አለማየሁ እና በአመልካች የፌዴራል ገቢዎች ጽ/ቤት አዳማ ቅርንጫፍ መካከል ስላለው የአፈጻጸም ክርክር በተመለከተ በአዳማ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ጎሮ ውስጥ የሚገኝ ፣ 200 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ሰፍሮ የሚገኝ የካርታ ቁጥር 5079/95 በ18/05/2003 የተሰጠ በፍርድ ባለዕዳ ወ/ሮ ራሔል አለማየሁ ዋሴ ሥም ተመዝግቦ የሚታወቅ የመኖሪያ ቤት በጨረታ ሽያጭ መነሻ ዋጋ ብር 3,677,680.20 (ሶስት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሰባ ሰባት ሺህ ስድስት መቶ ሰማንያ ብር ከ20/100) በሆነ በ22/12/2018 ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት በግልጽ ጨረታ ይሸጣል።

ተጫርቶ መግዛት የሚፈልግ ሰው ካለ ለአፈጻጸሙ ምክንያት የሆነውን ቤት የጨረታ መነሻ ዋጋ ግምት ¼ ኛ አስይዞ ሲፒኦ ይዞ ጨረታው ይካሄዳል በተባለበት ቀን እና ሰዓት በቦታው በመገኘት ተጫርቶ መግዛት የሚችል መሆኑን እናስታውቃለን።

የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የፍትሐብሔር

ጉዳይ ችሎት


Tender details

  • Deadline: 2026-08-28
  • Bid closing time: 12:00
  • Bid opening: 2026-08-28 12:00
  • Region: Oromia
  • Publishing entity: Adama City Higher Court
  • Bid bond: 25%
  • Published on: Addis Zemen (Jul 27, 2026)
  • Posted at: 2026-07-27T13:47:12.000Z
← Back to all tenders