Stationery and office consumables

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወረዳ 3 ፋይናንስ ፅ/ቤት የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር  Y/S/C/W/3/Fin.NCB001/2019 ዓ.ም.

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወረዳ 3 ፋይናንስ ፅ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለመጀመሪያ ዙር በወረዳው የተለያዩ ፅ/ቤቶች ለስራ አገልግሎት የሚውሉ

  • የተለያዩ የፅህፈት መሳሪያዎች ፣
  • የፅዳት ዕቃዎች ፣
  • የደንብ አልባሳት ፣
  • የተለያዩ ቋሚ ዕቃ፣
  • የተለያዩ የመኪና ዕቃዎች ፣
  • የተለያዩ ህትመት አገልግሎት፣
  • የተለያዩ መስተንግዶ አገልግሎት፣
  • የህዝብ ትራንስፖርት፣
  • የጭነት ትራንስፖርት፣
  • የተለያዩ የልብስ ስፌት ፣
  • የኤሌክትሮኒክስ ጥገና ፣
  • የፈርኒቸር ጥገና አገልግሎት፣
  • የሞንታርቦ ኪራይ አገልግሎት ፣
  • የጄኔሬተር ኪራይ አገልግሎት ፣
  • የድንኳን ኪራይ አገልግሎት እና
  • የዲኮር ኪራይ አገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት የሚፈልግ ሲሆን፡-

ሎት

የዕቃው ዓይነት

 

የጨረታ ማስከበሪያ የገንዘብ መጠን

001

የተለያዩ የፅህፈት መሳሪያዎች

ናሙና የሚቀርብበት

10000

00

002

የተለያዩ የጽዳት ዕቃዎች

ናሙና የሚቀርብበት

10000

00

003

የተለያዩ ደንብ አልባሳት

ናሙና የሚቀርብበት

10000

00

004

የተለያዩ ቋሚ ዕቃ

ናሙና በከለር ፎቶ የሚቀርብ

10000

00

005

የተለያዩ የመኪና ዕቃዎች

ናሙና በከለር ፎቶ የሚቀርብ

10000

00

006

የተለያዩ ህትመት

ናሙና የሚቀርብበት

5000

00

007

የተለያዩ መስተንግዶ

የአገልግሎት ዘመኑ ቅርብ የሆነ

5000

00

008

የህዝብ ትራንስፖርት ኪራይ

ጥራቱን የጠበቀ የተስተካከለ

5000

00

009

የጭነት ትራንስፖርት ኪራይ

ጥራቱን የጠበቀ የተስተካከለ

5000

00

010

የተለያዩ የደንብ አልባሳት ልብስ ስፌት

ጥራቱን የጠበቀ ስፌት

5000

00

011

የኤሌክትሮኒክስ ጥገና አገልግሎት

ጥራቱን የጠበቀ ጥገና

5000

00

012

የፈርኒቸር ጥገና አገልግሎት

ጥራቱን የጠበቀ ጥገና

5000

00

013

የሞንታርቦ ኪራይ አገልግሎት

ጥራቱን የጠበቀ የተስተካከለ

5000

00

014

የጄኔሬተር ኪራይ አገልግሎት

ጥራቱን የጠበቀ የተስተካከለ

5000

00

015

የድንኳን ኪራይ አገልግሎት

የተለያየ ጥራቱን የጠበቀ

5000

00

016

የዲኮር ኪራይ አገልግሎት

ጥራቱን የጠበቀ ያልተቀደደ

5000

00

 ስለዚህ፡- ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው

ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው እና በዘርፉ የተሰማሩ መሆን አለባቸው።

የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉ።

ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው።

የታደሰ የዘመኑን ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።

የመንግስት መ/ቤቶች ለሚያወጡት ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የአቅራቢዎች የተመዘገበ መሆን አለባቸው።

በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ክሊራንስ ማቅረብ የሚችልና በወቅቱ በማንኛውም ሁኔታ ያልተቀጣ (እንዲወዳደር ያልታፃደ) መሆን አለበት።

በዚህ ጨረታ አማራጭ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም።

በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ የጨረታ ውጤቱ እንደታወቀ ተመላሽ የሚሆን ከሎት 001 እስከ ሎት 005 ለተዘረዘሩት ብር 10000.00 አስር ሺህ ብር/ ከሎት 006  እስከ ሎት 016 ለተዘረዘሩት ብር 5000.00 /አምስት ሺህ ብር/ የተቀመጠውን የገንዘብ መጠን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ፋይናንስ ጽ/ቤት ተብሎ በተዘጋጀው ከባንክ በተመሰከረለት ሲ.ፒ.ኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለጸላቸው ሎት ያሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% ለየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወረዳ 3 ፋይናንስ ፅ/ቤት ተብሎ በተዘጋጀው ከባንክ በተመሰከረለት ሲ.ፒ.ኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።

ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነዶችና የዋጋ ማቅረቢያዎችን ፋይናንሻል/ ሰነዶችን በተለያየ ፖስታ ታሽጎ ለየብቻ ማቅረብ አለበት።

  1. ማንኛውንም ተጫራች የሚያስገባው ሰነድ የጨረታ ሰነድ ላይ ፣ ስርዝ ድልዝ ፤ በፍሉድ የጠፋ ሰነድ ፣ ዋጋ ያልተሞላበት ዝርዝር ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እናሳውቃለን።
  2. በጨረታ አሸናፊ የሆኑ ድርጅቶች ዕቃውን ወይም አገልግሎቱን በራሳቸው ትራንስፖርት የካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ፋይናንስ ፅ/ቤት ልዩ ቦታው ቤላ ጣሊያን ኤምባሲ አጠገብ በሚገኘው የአስተዳደሩ ግምጃ ቤት ወይም በክፍል 6 በፍላጎት መግለጫው በተጠቀሰው የማስረከቢያ ቦታ ድረስ በማምጣት ማስረከብ አለባቸው፤
  3. በጨረታ ሰነድ በክፍል 6 ውስጥ በሚገኘው የፍላጎት መግለጫ ላይ በሚገለፀው መሰረት ፋይናሻልና ቴክኒካል ሰነዶች ተገምግመው አሸናፊው ድርጅት ያሸነፈባቸውን የፅህፈት መሳሪያ፤ የፅዳት ዕቃ፣ የደንብ አልባሳት ቋሚ ዕቃ ሙሉ ለሙሉ አዘጋጅቶ ገቢ ከማድረጉ በፊት ከየዓይነቱ ናሙና ማቅረብ አለበት።
  4. ተጫራቾች ቤላ ጣሊያን ኤምባሲ አጠገብ በሚገኘው የወረዳ 3 አስተዳደር 1ኛ ፎቅ ግዢ የስራ ሒደት ቢሮ ቀርበው የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 400.00 /አራት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፤
  5. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 11፡00 ሰዓት ድረስ ጨረታው ክፍት ሆኖ ስለሚቆይ በወረዳው ግዢ የስራ ሒደት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 012 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  6. በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ 3፡30 ሰዓት ሲሆን በመ/ቤቱ 1ኛ ፎቅ ትንሹ ቢሮ ቁጥር 012 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፣
  7. የጨረታው መክፈቻ የስራ ቀን ካልሆነ ቀጥሎ ባለው መደበኛ የስራ ቀን ከላይ በተራ ቁ 6 ላይ በተጠቀሰው ሰዓት ይከፈታል።
  8. ዘግይተው የሚመጡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም።
  9. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በከፊልም ሆነ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ ፡- ከጣሊያን ኤምባሲ ፊት ስፌት በስተቀኝ ኮብልስቶን መንገድ 60 ሜትር ገባ ብሎ

በስ/ቁጥር፡- 0111 22 19 88 /0111 54 47 72

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የወረዳ 03 ፋይናንስ ጽ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-08-08
  • Bid closing time: 09:00
  • Bid closing (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-08-08 09:30
  • Bid opening (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Yeka sub City Admnistration woreda 03 finance & Development Office
  • Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
  • Bid document price: 400.00 ብር
  • Published on: Addis Zemen (Jul 28, 2026)
  • Posted at: 2026-07-28T09:21:01.000Z
← Back to all tenders