Stationery and office consumables
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ምስራቅ ጎህ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2019 ዓ.ም በጀት አመት ለቢሮና ለትምህርት አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ምስራቅ ጎህ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2019 ዓ.ም በጀት አመት ለቢሮና ለትምህርት አገልግሎት የሚውሉ፡-
- ቋሚ ዕቃዎች፣
- የፅህፈት መሳሪያ፣
- የደንብ ልብስ፣
- የፅዳት ዕቃዎች፣
- አላቂ የህክምና ዕቃዎች፣
- የኤሌክትሪክ ዕቃዎች፣
- የተለያዩ የህፃናት መጫወቻ ዕቃዎች፣
- የላብራቶሪ ዕቃዎችና
- የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታ የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- የታደሰ የንግድ ፍቃድና የዘመኑ ግብር የከፈሉ ለዚህም መረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- በመንግስት ንብረት ግዥ አስተዳደር ኤጄንሲ በዕቃ አቅራቢነት የተመዘገቡ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (vat) ተመዝጋቢ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ (Tin) ቁጥር ሊኖራቸው ይገባል፡፡
- ክሊራንስ፦ የዘመኑን ግብር የከፈሉበት ከግብር ሰብሳቢው መስሪያ ቤት ስለ ግብር አከፋፈል የሚሰጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ በየሎቱ 2% (ሁለት ፐርሰንት) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቧቸው ዕቃዎች ጥራትና ደረጃውን የጠበቀና ለዚህም ለእያንዳንዱ ዕቃ ናሙና ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ 100 (መቶ) ብር በመክፈል የጨረታ ሰነዱን በት/ቤቱ በግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን(ግዥ ክፍል) ቢሮ ቁጥር 4 መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ 15% ቫትን ጨምሮ በገዙበት ሰነድ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ በግልፅ መሙላት አለባቸው ይህን ያላደረጉ ተጫራቾች ቫትን አካተው እንደሞሉ ይቆጠራል፡፡
- ከላይ በተጠቀሰው የስራ ቀናት ዘወትር የስራ ሰአት በ/ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ለዚህ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ተጫራቾች (ህጋዊ) ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በጋዜጣ በወጣበት በ11ኛው የስራ ቀን ጠዋት 4፡00 ታሽጎ በዕለቱ ጠዋት 4፡30 ላይ በት/ቤቱ በግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 ይከፈታል፡፡
- ት/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ካዛንችስ ቶታል ፊት ለፊት ወደ አዋሬ መሄጃ መንገድ ምስ/ጎህ/2ኛ ደረጃ ት/ቤት
ስልክ ቁጥር፡- 0115-15-56-52
ምስራቅ ጎህ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-08-10
- Bid closing time: 10:00
- Bid closing (note): ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው የስራ ቀን ጠዋት 4፡00 ሰዓት
- Bid opening: 2026-08-10 10:30
- Bid opening (note): ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው የስራ ቀን ጠዋት 4፡30 ሰዓት
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Misrak Goh General Secondary School
- Bid bond: 2% በየሎቱ
- Bid document price: 100.00 ብር
- Published on: Addis Zemen (Jul 29, 2026)
- Posted at: 2026-07-29T08:22:28.000Z