Building and equipment maintenance

የድል በትግል ቅድመ አንደኛ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት የአጥር ጥገና፣ የመስኮት ጥገና እና የመምህራን ማረፊያ ሶፋ ጥገና በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታው ቁጥር 01/2019

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጉለሌ ክ/ከተማ ት/ፅ/ቤት ወረዳ 01 ስር የሚገኘው የድል በትግል ቅድመ አንደኛ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ለ2019 ዓ.ም በጀት ዓመት በውስጥ ገቢ በጀት ለት/ቤቱ አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ስራዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራትይፈልጋል፡፡

  • ሎት 1፡- የአጥር ጥገና
  • ሎት 2፡- የመስኮት ጥገና
  • ሎት 3፡- የመምህራን ማረፊያ ሶፋ ጥገና

በዚህ ጨረታ ለመወዳደር የምትፈልጉና ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የምታሟሉ ህጋዊ ተወዳዳሪዎች፡-

  1.  በመንግስት ዕቃ አቅራቢነት ዝርዝር የተመዘገቡ የምስክር ወረቀት ያላቸው እና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ እና በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው።
  2.  በጥቃቅን እና አነስተኛ በአምራችነት ተደራጅተው የሚመጡ ተወዳዳሪዎች በሚያቀርቡት የዋስትና ደብዳቤ መሰረት የሚስተናገዱ ይሆናል።
  3. የእቃዎች ዋጋ 15% ቫት ተጨምሮ ይቅረብ፣ ባይቀርብ እንደተጨመረ ሆኖ የሚሰራ ይሆናል፡፡
  4. ተጫራቾች የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታውን ዝርዝር መረጃ የያዘ ሰነድ ከት/ቤቱ ፋ/ግ/ን/አስ/ደጋፊ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 4 በመምጣት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
  5.  ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙት ሰነድ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ ቦታ በግልፅ መሙላት አለባቸው።
  6. ተጫራቾች ለሎት1፡15,000.00 ለሎት2፡15,000.00 ለሎት3፡15,000.00 የጨረታ ማስከበሪያ ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው።
  7. ተጫራቾች የተመረጡ እቃዎች እና ናሙና ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ አለባቸው፡፡
  8.  ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን በቢሮ ቁጥር 05 ማስገባት ይችላሉ፡፡
  9.  አሸናፊ ሆነው የተመረጡ ድርጅቶች የአሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ የውል ማስከበሪያ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  10. አሸናፊው ተጫራች ያሸነፈባቸውን እቃዎች በራሳቸው የትራንስፖርት ወጭ ት/ቤቱ ንብረት ክፍል ድረስ ማምጣት አለባቸው፡፡ ት/ቤቱ ተጨማሪ የስራውን 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብት አለው፡፡
  11. ጨረታው ማስታወቂያው በወጣበት 10ኛው ቀን 11፡30 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ በ3፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች ቢገኙም ባይገኙም ቢሮ ቁጥር 01የሚከፈት ይሆናል፡፡
  12.  ት/ቤቱ የተሻለ መንገድ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ፦ ጉለሌ ክ/ከተማ ሽሮሜዳ ከስፔን ኤምባሲ አጠገብ

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡-0111-54-20-95

የድል በትግል ቅድመ አንደኛ አንደኛ

እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-08-08
  • Bid closing time: 17:30
  • Bid closing (note): ጨረታው ማስታወቂያው በወጣበት 10ኛው ቀን 11፡30 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-08-10 09:30
  • Bid opening (note): ጨረታው ማስታወቂያው በወጣበት 11ኛው ቀን 3፡30 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Del Betegel Elementary School
  • Buyer address: ጉለሌ ክ/ከተማ ሽሮ ሜዳ ከስፔን ኤምባሲ አጠገብ
  • Bid bond: 15,000.00 ብር ለእያንዳንዱ ሎት
  • Bid document price: 200.00 ብር
  • Published on: Addis Zemen (Jul 29, 2026)
  • Posted at: 2026-07-29T08:27:29.000Z
← Back to all tenders