Stationery and office consumables
የጅማ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት የተለያዩ ቋሚና አላቂ የቢሮ እቃዎችን፣ የጽህፈት መሣሪያዎችን፣ የጽዳት እቃዎችን፣ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን እና ጎማ እና ባትሪ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
Description
የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
የጅማ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት በዞን ደረጃ ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉትን
- የተለያዩ ቋሚና አላቂ የቢሮ እቃዎችን፣
- የጽህፈት መሣሪያዎችን፤
- የጽዳት እቃዎችን ፣
- የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን እና
- ጎማ እና ባትሪ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ከዚህ በታች የቀረቡትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሣተፍ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን ። በዚህ መሠረት
ተወዳዳሪዎች ማሟላት የሚገባቸው መመዘኛዎች :-
- ለሥራ ዘርፉ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ
- ግብር ከፋይ ምዝገባ ማለትም Tin No ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችልሉ፣
- በአቅራቢነት ለመሣተፍ የተመዘገበ ከፌዴራል ገንዘብ ሚ/ር ወይም ከክልል የገንዘብ ቢሮ የተሰጠ የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል፣
- ተወዳዳሪዎች የተጨማሪ እሴትታክስ /VAT/ለመሰብሰብ የተመዘገቡና የMAI ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ፣
- የዘመኑን ግብር የከፈሉና Tax ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት የጨረታውን ሠነድ ለእያንዳንዱ ጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 500.00 ( አምስት መቶ) በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት ጽ/ቤቱ ግዥ ቡድን ቢሮ ቁጥር 6 መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለጽህፈት መሣሪያዎች የኢትዮጵያ ብር 10,000.00 ( አስር ሺህ ) ብር፣ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችና ጎማ እና ባትሪ እቃዎች የኢትዮጵያ ብር 15000.00 (አስራ አምስት ሺህ) እና ለጽዳት እቃዎች ደግሞ ብር 7000.00(ሰባት ሺህ) በጅማ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት ስም በባንክ በተመሠከረለት ሲፕኦ (CPO) ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች የሚያቅርቡት መወዳደሪያ ዋጋ ታክስን (VAT) አጠቃሎ የተሠራና በአፋን ኦሮሞ በተዘጋጀው የጨረታ ሠነድ ላይ ተዘጋጅቶ በቀረበው ፎርማት መሠረት በታይፕ ወይም በቀለም ሞልተው መመለስ አለባቸው :: የጨረታውን ሠነድ ሞልተው በታሸገ ፖስታ አድርገው በተዘጋጀው የጨሪታ ሣጥን ማስገባት አለባቸው።
- የቴክኒካል ዶክመንት ኦርጅናል ሲፒኦ (CPO) ጋር ታሽጎ ቴክኒካል ኮፒ ዶክመንት ጋር የጨረታ ዓይነት ተገልጾ በሁለቱ ፖስታ ላይ የድርጅቱ ስምና አድራሻ ተፅፎ በአንድ ፖስታ ይገባል ።
- የፋይናንሻል ዶክመንት ኦርጅናል በፖስታ ታሽጎ ከፋይናንሻል ኮፒ ዶክመንት ጋር የጨረታ ዓይነት ተገልጾ በሁለቱ ፖስታ ለይ የድርጅቱ ስምና አድራሻ ተፅፎ በአንድ ፖስታ ይገባል ።
- የጨረታ ሣጥን መዝጊያና መክፈቻ ሰዓቱን እና ቀን አስመልክቶ ሠነዶቹን መሸጫ ቀን ካበቃበት ዕለት በኋላ በሚቀጥለው የመጀመሪያ የሥራ ቀን ከጠዋቱ ልክ በ4፡00 ሠዓት የጨረታ ሣጥን ተዘግቶ በዚያንኑ ቀን ልክ በ4፡30 ይከፈታል ።
- ጽህፈት ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን ለመግዛት ሲመጡ ከላይ 1-5 ተራ ቁጥር የተጠቀሰውን ቴክኒካል መረጃ እና
- ኮፒ መያዝ አለባቸው።
- ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 047 111 1193 ወይም 047 111 0380 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
የጅማ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-08-11
- Bid closing time: 10:00
- Bid closing (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ቆይቶ በሚቀጥለው የመጀመሪያ የሥራ ቀን ከጠዋቱ ልክ በ4፡00 ሠዓት
- Bid opening: 2026-08-11 10:30
- Bid opening (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ቆይቶ በሚቀጥለው የመጀመሪያ የሥራ ቀን ከጠዋቱ ልክ በ4፡30 ሠዓት
- Region: Oromia
- Publishing entity: JImma Zone FEDB
- Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
- Bid document price: 500.00 ብር
- Published on: Addis Zemen (Aug 02, 2026)
- Posted at: 2026-08-03T11:02:40.000Z