Property and building foreclosure
ወጋገን ባንክ አ.ማ መጋዘን እና የተሽከርካሪ በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Description
ወጋገን ባንክ አ.ማ
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ
ቁጥር፡ ወጋገን 038/2018
ወጋገን ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 1147/2011፣ 97/90 እና 216/92 መሰረት ከዚህ በታች የቀረቡትን የመያዣ ንብረቶች በግልጽ የሐራጅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
የማይንቀሳቀስ ንብረት የሀራጅ ጨረታ ዝርዝር
|
ተ.ቁ |
የተበዳሪው ስም |
አበዳሪው ቅርንጫፍ |
ንብረት አስያዥ |
የንብረቱ አድራሻ |
የቦታው ስፋት |
የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ ቁጥር |
የንብረቱ ዓይነት/የይዞታ አገልገሎት
|
የጨረታ መነሻ ዋጋ
|
ጨረታው የሚከናወንበት ቀን እና ሰዓት
|
||
|
ከተማ/ ክልል |
ክ/ከተማ/ከተማ/ዞን |
ወረዳ/ ቀበሌ |
|||||||||
|
2 |
ኤች ኤም አር ትሬዲንግ ኃላ/የተ/ የግ/ማህበር |
ስታዲየም |
ተበዳሪው |
ኦሮሚያ |
ሸገር ከተማ አስ/ር |
ሱሉልታ
|
5,178.8 ካ/ሜትር |
OR000 010264 09003 |
መጋዘን
|
13,738,127.53
|
ነሀሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጧቱ 3፡00 እስከ6፡00 ሰዓት |
የተሽከርካሪ የሀራጅ ጨረታ ዝርዝር
|
ተ.ቁ |
የተበዳሪው ስም |
ንብረት አስያዥ |
አበዳሪ ቅርንጫፍ |
የተሽከርካሪ ዓይነት |
የሰሌዳ ቁጥር |
የሻንሲ/ሴሪያል ቁጥር
|
የሞተር ቁጥር
|
ዘመን
|
የነዳጅ አይነት
|
የጨረታ መነሻ ዋጋ |
ጨረታው የሚከናወንበት ቀን |
|
|
ቀን |
ሰዓት |
|||||||||||
|
1 |
ኤን ኬይ ኤች ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/የግ/ ማህበር |
ተበዳሪው
|
ሰባራ ባቡር
|
ድርብ ተግባር (ፒክአፕ)
|
አአ-03-B42216 |
AHTK B8CD X02981400
|
2GD-0 984997
|
2021 |
ናፍጣ |
3,500,000.00
|
ነሀሴ 11 2018 ዓ.ም |
ከጧቱ 3፡00-6፡00 ሰዓት |
ማሳሰቢያ
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የጨረታ መነሻ ዋጋ 1/4 (አንድ አራተኛ) በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ (C.P.O) በወጋገን ባንክ አ.ማ ስም በማሰራት በጨረታው ዕለት በመቅረብና በመመዝገብ በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ።
- የጨረታ አሸናፊ ከባንኩ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ከተሰጠው ቀን ጀምሮ ቀሪውን ገንዘብ በ15 /አስራ አምስት/ ቀናት ውስጥ አጠናቆ መክፈል ይኖርበታል። ባይከፍል ግን የሐራጁ ውጤት ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፣ ላላሸነፉት ተጫራቾች ግን ያስያዙት ሲፒኦ ወዲያዉኑ ይመለስላቸዋል።
- ጨረታውን ላሸነፈ፤ የባንኩን የብድር ፖሊሲ፤ መመሪያ እና ቅድመ ሁኔታ ለሚያሟላ እንዲሁም ተጨማሪ የመያዣ ንብረት ለሚያቀርብ ተጫራች፤ ባንኩ በብድር መመሪያ መሰረት ብድር ሊያመቻች ይችላል።
- የተጫራቾች የምዝገባ ሰዓት፤ ከጧቱ 3፡00 - 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ሲሆን ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ለንብረቶቹ የሚመደበው የጥሪ ሰዓት 30 ደቂቃ ብቻ ነው። ሆኖም የጨረታው መጠናቀቂያ ሰዓት ድረስ አሸናፊው ካልተለየ አሸናፊ እስኪለይ ድረስ ጨረታው ይቀጥላል።
- በጨረታው የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ጨረታውን ካካሄደው ከባንኩ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ሲደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል።
- ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል።
- ጨረታው የሚካሄደው በወጋገን ባንክ ዋና መስርያ ቤት ህንጻ 13ኛ ወለል ላይ በሚገኘው የመሰብሰብያ አዳራሽ ይሆናል።
- ለሀራጅ ጨረታ የቀረቡትን ንብረቶች ለመጎብኘት የሚፈልግ ተጫራች የጨረታው ቀን ከመድረሱ በፊት ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በማስያዝ መጎብኘት ይችላል።
- ተበዳሪው /ንብረት አስያዥ/ ወይም ሁለቱም በጨረታው ቀን እና ሰዓት በቦታው ላይ መገኘት ይችላሉ። ነገር ግን ተበዳሪው /ንብረት አስያዡ/ በጨረታ ቀን እና ሰዓት በቦታው ባይገኝ ጨረታውበሌለበት ይካሄዳል። ከዚህ በተጨማሪ ጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች ወይም የተጫራቾች ህጋዊ ተወካዮች ብቻ ናቸው።
- ማንኛውንም ለመንግስት ሊከፈል የሚገባውን ክፍያ ተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ የጨረታው አሸናፊ የሚከፍል ይሆናል።
- ለበለጠ ማብራሪያ ወይም የጉብኝት ቀጠሮ ለማመቻቸት ወጋገን ባንክ አ.ማ የብድር ማስመለስ ዳይሬክቶሬት 011-558-1837፣ መደወል ይችላሉ።
- ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም።
ወጋገን ባንክ አ.ማ
Tender details
- Deadline: 2026-09-01
- Bid closing time: 12:00
- Bid closing (note): የሐራጁ መዝጊያ ቀንና ሰዓት የተለያየ ነው
- Bid opening: 2026-09-01 12:00
- Bid opening (note): የሐራጁ መክፈቻ ቀንና ሰዓት የተለያየ ነው
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Wegagen Bank S.C.
- Bid bond: 25%
- Published on: Reporter (Aug 02, 2026)
- Posted at: 2026-08-03T12:21:39.000Z