Stationery and office consumables

የሀድያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የጽህፈት መሣሪያና የጽዳት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

የሀድያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በዞኑ ለሚገኙ ሴክተሮችና መምሪያዎች የሚያስፈልጉ የተለያዩ ዓይነት፡-

  • ሎት 1- የጽህፈት መሣሪያና
  • ሎት 2 - የጽዳት ዕቃዎች

በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

በዚሁ መሠረት ተጫራቾች፡-

1ኛ. በመስኩ የታደሰ ንግድ ፈቃድ

2ኛ, የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር

3ኛ. የቫት ተመዝጋቢነት ሠርትፍኬት

4ኛ. የዕቃና አገልግሎት አቅራቢነት ሰርትፍኬት ያላቸው ድርጅቶች፤ በሀድያ ዞን ፋ/መምሪያ ቢሮ ቁጥር 17 በአካል በመቅረብ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ብር 100/አንድ መቶ ብር/ በመክፈል እንድትገዙና ተጨራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሎት-1 30,000 ሎት 2 20,000 ብር በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ማስያዝ የሚጠበቅባቸው ሲሆን የጨረታ መወዳደሪያ መምሪያው ባዘጋጀው ፎርማት ላይ ብቻ በመሙላት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የመወዳደሪያ ፖስታዎችን ኦርጅናልና ኮፒ በማሸግ ቢሮ ቁጥር 17 ላይ በሚገኘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እንድታስገቡና ጨረታውም በ16ኛው ቀን ከሠዓት 8፡00 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥን ታሽጎ በ8፡30 ላይ የሚከፈት ሲሆን ቀኑ የእረፍት ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ቦታና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡

መሥሪያ ቤቱ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0461784281/0465552337 ደውሎ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን፡፡

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት

የሀድያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ


Tender details

  • Deadline: 2026-08-24
  • Bid closing time: 14:00
  • Bid closing (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከሠዓት 8፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-08-24 14:30
  • Bid opening (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከሠዓት 8፡30 ሰዓት
  • Region: Central Ethiopia
  • Publishing entity: Hadiya Zone Finance Bureau
  • Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
  • Bid document price: 100.00 ብር
  • Published on: Addis Zemen (Aug 09, 2026)
  • Posted at: 2026-08-10T07:55:28.000Z
← Back to all tenders