Textile, Garments and Uniforms

ኦሮሚያ ባንክ ለጥበቃ ሰራተኞች የሚሆን ጃኬት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ
የደንብ ልብስ ግዥ ግልጽ ጨረታ
የጨረታ ቁጥር፡ OT/06/2026-27

ኦሮሚያ ባንክ ለጥበቃ ሰራተኞች የሚሆን ጃኬት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል::

ስለዚህ በሥራ ዘርፉ የተሰማራችሁ ድርጅቶች ከታች በሰንጠረዥ ውስጥ በተገለፀው መልክ ለማቅረብ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን::

ዝርዝር

መለኪያ

ብዛት

 

መግለጫ

 

ጃኬት

በቁጥር

 

613

 

በተለያየ ልኬት ሆኖ በኔቪ ብሉ ከለር (Navy-Blue Color and Different Size)

1. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 1,000.00 (ብር አንድ ሺህ) በባንኩ ዋና መ/ቤት ሕንፃ ስር በሚገኘው የባንኩ አፍሪካ ጎዳና ቅርንጫፍ በመክፈል ከታች ከተጠቀሰው አድራሻ ከነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የጨረታ ሰነድ በመግዛት መሣተፍ ይችላሉ::

አድራሻ
ግዥ እና ውል አስተዳደር ዋና ክፍል
የባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት ዘጠነኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 9-002
ቦሌ መንገድ ከጌቱ ንግድ ማዕከል አጠገብ
ስልክ ቁጥር 0115572098/95

2. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ሰነድ በታሸገ ፖስታ በማድረግ ከናሙና ጋር እስከ ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ከላይ በተገለፀው አድራሻ ለዚሁ አላማ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ::

3. ጨረታው በተመሣሣይ ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል::

4. ባንኩ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

ኦሮሚያ ባንክ


Tender details

  • Deadline: 2026-08-27
  • Bid closing time: 14:00
  • Bid opening: 2026-08-27 14:30
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Oromia Bank S.C.
  • Bid document price: 1000 (አንድ ሺህ ብር)
  • Published on: Reporter (Aug 16, 2026)
  • Posted at: 2026-08-17T12:18:11.000Z
← Back to all tenders