Textile, Garment and Leather

ፊዩቸር ታለንት አካዳሚ አ.ማ. ብቁና በህጋዊ መንገድ የተመዘገቡ ተጫራቾችን ከቅድመ መደበኛ (ኬጂ) እስከ 12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች መደበኛ የትምህርት ቤት ዩኒፎርም እና የስፖርት አልባሳት ለማሰራት ለማቅረብና ለማድረስ/ለማሰራጨት ተጫራቾች እንዲወዳደሩ ይጋብዛል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

1.ፊዩቸር ታለንት አካዳሚ አ.ማ ብቁና በህጋዊ መንገድ የተመዘገቡ ተጫራቾችን ከቅድመ መደበኛ (ኬጂ) እስከ 12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች መደበኛ የትምህርት ቤት ዩኒፎርም እና የስፖርት አልባሳት ለማሰራት ለማቅረብና ለማድረስ ለማሰራጨት ተጫራቾች እንዲወዳደሩ ይጋብዛል። ተጫራቾች በሎት 1 (የስፖርት ዩኒፎርም) እና በሎት 2 የተማሪዎች የደንብ ልብስ መወዳደር ይችላሉ፣ ዝርዝር ቴክኒካዊ መስፈርቶችና መጠኖች በጨረታ ሰነዱ ውስጥ ተካትተዋል።

2. በስራው ህጋዊ የንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን)፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ምዝገባ እና የግብር ክሊራንስ ያላቸው ብቁ ተጫራቾች፣ ከዚህ በታች በተመለከተው አድራሻ ብር 1000 (አንድ ሺህ ብር) የማይመለስ በመክፈል ከ14/12/2018 ጀምሮ በስራ ሰዓት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።

አድራሻ

ፊዩቸር ታለንት አካዳሚ ወሎ ሰፈር ጎርጎርዮስ አደባባይ ወደ ቦሌ ሚካኤል በሚወስደው መንገድ ዋና ግቢ ቢሮ ቁጥር 4

ስልክ / ኢሜይል

0966-14-94-22

የጨረታ ሰነድ ዋጋ

ብር 1000 (አንድ ሺህ ብር) (የማይመለስ)

የጨረታ ማስከበሪያ

100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) ለአንድ ሎት በሲፒኦ (በፊዩቸር ታለንት አካዳሚ . ስም)

የጨረታ ማስገቢያ የመጨረሻ ቀን

ነሐሴ 21 ቀን 2018 . ከጠዋቱ 400 እስከ 430 ብቻ

የጨረታ ማስገቢያ አድራሻ

ፊዩቸር ታለንት አካዳሚ ወሎ ሰፈር ጎርጎርዮስ አደባባይ ወደ ቦሌ ሚካኤል በሚወስደው መንገድ ላይ ዋና ግቢ ቢሮ ቁጥር 7

የጨረታ መክፈቻ

ነሐሴ 21 ቀን 2018 . 430 ወዲያውኑ፣ በተመሳሳይ ቦታ፣ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ይከፈታል

የጨረታ ሰነድ መሸጫ ግዜ

ከነሐሴ 14 ቀን 2018 . እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2018 . በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 200-1100 ሰዓት እና ቅዳሜ 200-600 ሰዓት

3. ተጫራቾች አስፈላጊውን የጨረታ ማስከበሪያ አያይዘው ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ በተጠቀሰው ቀነ-ገደብ ውስጥ ሰነዳቸውን ማስገባት አለባቸው፡፡ ከቀነ-ገደቡና ሰዓት በኋላ የሚደርሱ ጨረታዎች ተቀባይነት የላቸውም፡፡ ጨረታው በቀነ-ገደቡና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል።

4. አካዳሚው ጨረታዎችን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ፊዩቸር ታለንት አካዳሚ


Tender details

  • Deadline: 2026-08-27
  • Bid closing time: 10:30
  • Bid opening: 2026-08-27 10:30
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Future Talent Acadamy S.C
  • Buyer address: ወሎ ሰፈር ኢትዮ ቻይና መንገድ ጎርጎሪዎስ አደባባይ ወረድ ብሎ
  • Bid bond: 100,000.00 ብር ለአንድ ሎት
  • Bid document price: 1,000.00 ብር
  • Published on: Reporter (Aug 19, 2026)
  • Posted at: 2026-08-19T11:59:12.000Z
← Back to all tenders