Vehicle

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዓለም ገና መ/ጥ/ዲስትሪክት 25 ሰው መጫን የሚችል የሠራተኞች ሰርቪስ (አውቶብሶች) በቁጥር 6 (ስድስት) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል

Description

አስቸኳይ የጨረታ ማስታወቂያ ጨ-47-2018

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዓለምገና መ/ጥ/ዲስትሪክት ስር ለሚገኙ ፕሮጀክቶችየሚሆን 25 ሰው መጫን የሚችል የሠራተኞች ሰርቪስ (አውቶብሶች) በቁጥር 6 (ስድስት)በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል።

ስለሆነም በዚህ ጨረታ ስመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች ያለውን ሁኔታ በማሟላት መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ያሳውቃል።

ተ/ቁ

መስፈርት

ዝቅተኛ መስፈርት

1

የተሽከርካሪ ዓይነት

አውቶብስ/ኮስትር/ ዓይነት ወይም ተመጣጣኝ

2

የተሳፋሪው መቀመጫ አቅም

ቢያንስ 25

3

የተሽከርካሪ ሁኔታ

ደህንነቱ የተጠበቀ ንፁህና ለመንገድ ጉዞ ተስማሚ

4

የምርት (የስሪት) ዘመን

እ.ኤ.አ 2015 እና ከዚያ በላይ

5

አየር ማቀዝቀዣ

ግዴታ /አማራጭ/

6

የመቀመጫ ቀበቶ

በአምራቹ የተገጠመ ከሆነ ግዴታ ነው

7

ምዝገባ

የሚያገለግል የኢትዮጵያ ተሽከርካሪ ምዝገባ

8

የመንገድ ብቃት

የሚያገለግል የተሽከርካሪ ምርመራ/ማረጋገጫ/

9

ኢንሹራንስ

የሚያገለግል የኢንሹራንስ ሽፋን

10

አሽከርካሪ

ብቃት ያለውና ተገቢውን የመንጃ ፍቃድ ያለው

 

  1. ተጫራቾች በሥራ ዘርፍ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ አቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ የተጨማሪ እሴት ታክስ ማስረጃ ያላቸው እንዲሁም የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሠርተፍኬት ማስረጃ ከጨረታው ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ።
  2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት አለምገና በሚገኘው የመ/ቤቱ ፋይናንስ ክፍል የማይመለስ 500.00 (አምስት መቶ) ከፍለው የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ከግዥ አቅርቦትና ንብረት አስተዳደር ቡድን ቢሮ መውሰድ ይችላል።
  3. ተጫራቾች የሚጫረቱትን ተሽከርካሪ በመግለፅ ከተዛማጅ ማስረጃዎቻቸው ጋርሁሉንም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ለዚህ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን በግዥ አቅርቦትና ንብረት አስተዳደር ቡድን ገቢ የሚያደርጉበት የመጨረሻ ቀን 30/12/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ድረስ ብቻ ነው።
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 20,000.00 የባንክ ዋስትና ወይም CPO ብቻ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማስገባት።
  5. የጨረታ ሳጥኑ 30/12/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4፡30 በዓለምገና መ/ጥ/ዲስትሪክት የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል።
  6. ተጫራቾች አላስፈላጊ ድርጊት ላለመፈፀም ቃል የሚገቡበት ቅፅ ሞልተውና ፈርመው ከመወዳደሪያ ሰነዶቻቸው ጋር ለማቅረብ ፈቃደኛ መሆን አለባቸው።
  7. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ማሳሰቢያ፡- አውቶብሱ ተቀያሪ ጎማ ፣እሳት ማጥፊያ፣የመጀመሪያ ዕርዳታ መስጫ ኪት እና የአደጋ ጊዜ መውጫ ሊያሟላ ይገባል።

ለበለጠ መረጃ

በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአለምገና መ/ጥ/ዲስትሪክት

ስልክ ቁጥር 011-387-10-28/0912117911

አድራሻ፡- ዓለምገና ቀበሌ 02 ከአዲስ አበባ ወደ ሰበታ መውጫ

በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአለምገና መ/ጥ/ዲስትሪክት


Tender details

  • Deadline: 2026-09-05
  • Bid closing time: 10:00
  • Bid opening: 2026-09-05 10:30
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Ethiopian Roads Authority Alemgena Road Maintenance District
  • Buyer address: ዓለምገና ቀበሌ 02 ከአዲስ አበባ ወደ ሰበታ መውጫ በስተቀኝ በኩል
  • Bid bond: 20,000.00 ብር
  • Bid document price: 500.00 ብር
  • Published on: Addis Zemen (Aug 21, 2026)
  • Posted at: 2026-08-21T10:56:39.000Z
← Back to all tenders