Textile, Garments and Uniforms

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የም/ባሌ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት በዞኑ ስር ለሚገኙ የመ/መስሪያ ቤቶች የተለያዩ እቃዎችን ለመግዛት ይፈልጋል

Description

ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የም/ባሌ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት በዞኑ ስር ለሚገኙ የመ/መስሪያ ቤቶች በ2019 ዓ.ም በጀት የመጀመሪያ ዙር ግዥ፤

  • 1) የደንብ ልብስ ጫማ እና የስፌት አገልግሎት
  • 2) የፅህፈት መሳሪያ፤
  • 3) የፅዳት እቃ፣
  • 4) አላቂ የቢሮ እቃዎች፣
  • 5) የግንባታ እቃዎች
  • 6) የመኪና ጎማ እና ባትሪ፤
  • 7) ቋሚ እቃ (ፈርኒቸርና ኤሌክትሮኒክስ)፤
  • 8) የሞተር ሳይክሎች 150 cc እና ከዛ በታች፤
  • 9) የቢሮ ውስጥ ምንጣፎችና ማስዋቢያ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

የመወዳደሪያ መስፈርት

  • የንግድ ምዝገባ ቁጥር ያለው ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
  • በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገበ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
  • የ2018 ግብርን ከፍሎ ያጠናቀቀ። የንግድ ፍቃዱን ለ 2019 የስራ ዘመን ያሳደሰ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
  • ከግብር ክፍያ ነፃ ስለመሆኑ ማስረጃ ክሊራንስ ማቅረብየሚችል።
  • የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያለው፤ የቫት ተመዝጋቢ የሆነ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
  • የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ CPO 100,000 (አንድ መቶ ሺህ) ብር በምስራቅ ባሌ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት ስም አሰርተው በእጃቸው ይዘው መቅረብ ሲኖርባቸው ከ (2 አመት) ወዲህ |አዲስ የተደራጁ ማ ራት ካደራጃቸው አካል የጨረታ ማስከበሪያ የዋስትና ደብዳቤ በእጃቸው ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • የተደራጁ ማህበራት ካደራጃቸው አካል ህጋዊ መህበር መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በህትመት (ሃርድ ኮፒ) ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 (አስራ አምስት) የስራ ቀናት ከምስራቅ ባሌ ዞን ገቢዎች መስሪያ ቤት የማይመለስ 300 ( ሶስት መቶ) ብር በመክፈል መግዛት ይችላል።
  • ጨረታውን ተወዳድሮ ያሸነፈው የሚፈርመው ውል ለግማሽ አመት ወይም ለ 6 ወር እንደሚቆይ ማወቅ ሲኖርበት፤ይህንን አውቆ ውል ለመግባት ፍቃደኛ የሆነ።
  • ጨረታውን ተወዳድሮ ያሸነፈው ተጫራች የውል ማስከበሪያ ከተሰጠው ትእዛዝ ውስጥ 10% CPO ለማስያዝ ፍቃደኛ የሆነ።
  • የተለያዩ ተቀናናሽ ከፍያዎችን ማለትም የቲኦቲ እና ከቫት 15 % ግማሹን (7.5) ለመከፈል ፍቃደኛ የሆነ።
  • ተጫራች ጨረታውን ማሸነፉ ከተገለፀ እና ትእዛዝ ከተቀበለ በኋላ ባሉት በተከታታይ 15 /አስራ አምስት/ ቀናት ውስጥ ምስራቅ ባሌ ዞን ገንዝብ ጽ/ ቤት ማቅረብ ይኖርበታል።
  • ተወዳዳሪዎች ለውድድር ሲቀርቡ ቴክኒካል ማስረጃቸውን ዋናውንና፤ ኮፒውን ለየብቻ በሰም አሽገው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ተጫራች ፋይናንሺያል ማስረጃ ዋናውንና ኮፒውን ለየብቻ በሰም በማሸግ ሙሉ ሰነዱን፤የመወዳደሪያ ዋጋቸውን በጥንቃቄ በግልፅ በማስቀመጥ፤ ስም፣ ፊርማ፣ የስልክ ቁጥራቸውን ፣ የድርጅታቸውን አድራሻ ፣ማህተም ፣ በመሙላት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • የጨረታ ሰነዱ ማቅረቢያ ጊዜ የሚያበቃው ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት በ 11ኛ (አስራ አንደኛው) የስራ ቀን ከጠዋቱ 3:00 ሲሆንጨረታው የሚከፈተው በዚያው ቀን ከጠዋቱ 3:30 ተወዳዳሪዎች ህጋዊ ወኪሎች፤የግዥ ኮሚቴዎች፤ ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ባሉበት በምስራቅ ባሌዞን ገንዘብ ጽ/ቤት፣ በግዢ ክፍል ቁጥር 8 ውስጥ በግልጽ ይሆናል።
  • የጨረታ ሰነዱ የሚከፈትበት ቀን ባጋጣሚ የስራ ቀን ባይሆን በቀጣዩ የስራ ቀን የሚከፈት ይሆናል።
  • የጨረታ ሳጥኑ ከታሸገ በኋላ ዘግይቶ የሚቀርብ ማንኛውም የመወዳደሪያ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፤ የዋጋ ማሻሻል አይቻልም።
  • ተጫራቾች መጫረት የሚችሉት ባላቸው የንግድ ፍቃድ ዘርፍ ብቻ መሆኑን ማወቅ ይኖርባቸዋል። ከንግድ ፍቃዳቸው ዘርፍ ውጭ መወዳደር አይችሉም።
  • ገዥው መስሪያ ቤት የግዥውን መጠን በ20 ፐርሰንት ቀንሶ ወይም ጨምሮ ሊገዛ ይችላል።
  • ገዥው መስሪያ ቤት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
  • ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የእቃ ሞዴል የመሙላት ግዴታ አለባቸው የሚያቀርቡትን እቃ ሞዴል ካልሞሉ ዋጋቸው ተቀባይነት አይኖረውም።
  • አቅራቢዎች ሚገጣጠሙ የሚታሰሩ ንብረቶችን (ወንበሮች፡ሼልፎች ጠረጴዛዎች) አስተካክለው ገጥመው ለንብረት ክፍል ማስረከብ ይኖርባቸዋል።
  • የላፐቶፕ ኮምፒውተር ፡ አሸናፊ ተወዳዳሪ ለ1 ወር የሚቆይ የዋስትና ጊዜ መኖሩን አውቆ መወዳደር ይኖርባቸዋል። እቃው ቸግር ካለበት የመመለስ ግዴታ አለባቸው የውል ማስከበሪያቸውም የዋስትና ጊዜው ሲያበቃ የሚመለስ መሆኑን መገንዘብ ይጠበቅባቸዋል።

ማሳሰቢያ

  • ተጫራች ሌሎች ዝርዝር ሁኔታዎችን ከጨረታ ሰነድ ውስጥ ማግኘት ይችላሉ።
  • ለአቅራቢው ክፍያ የሚፈጸመው በውድድሩ መሰረት ጥራት ያለውን እቃ በተፈለገው ጊዜ፤ መጠን፤ ቦታ፤ አይነት ሲያቀርብ በግዥ ኮሚቴዎች በሚመለከታቸው _ ባለሙያ አካላት ታይቶ ርክክብ ከተደረገና ህጋዊ ደረሰኝ ከተቆረጠ ቦኋላ ይሆናል።

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 10 37 30 81/ 09 13 81 00 62 / 09 17 55 77 27
/ 09 75 89 67 20 ደውለው ማጣራት ይችላሉ።
የምስራቅ ባሌ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት፣
ጊኒር


Tender details

  • Deadline: 2026-09-12
  • Bid closing time: 12:00
  • Bid closing (note): ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ 11ኛ (አስራ አንደኛው) የስራ ቀን ከጠዋቱ 3:00
  • Bid opening: 2026-09-12 12:00
  • Bid opening (note): ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ 11ኛ (አስራ አንደኛው) የስራ ቀን ከጠዋቱ 3:30
  • Region: Oromia
  • Publishing entity: East Bale Zone Finance Office
  • Bid bond: 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ ብር)
  • Bid document price: 300.00 (ሶስት መቶ ብር)
  • Published on: Addis Zemen (Aug 31, 2026)
  • Posted at: 2026-09-01T12:07:33.000Z
← Back to all tenders