Textile, Garments and Uniforms

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል የተለያዩ እቃዎችን መግዛት ይፈልጋል

Description

የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር አ/አ/ከ/አ/ስነ/ሴ/ተ/ክ/ማ/ማ(01/001-012/2019)

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል በ2019 በጀት ዓመት በ 12 ሎት የተከፈሉ ግዥዎችን ለአንደኛ ዙር በግልፅ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

ሎት ቁጥር

 

የሚገዛው እቃ/አገልገሎት

 

የጨረታ ማስከበሪያ መጠን

 

ሎት 1

 

የደንብ ልብስ ግዥ

 

50,000.00 cpo

 

ሎት 2

 

አላቂ የቢሮ ዕቃዎች ግዥ

 

30,000.00 cpo

 

ሎት 3

 

የህትመት ግዥ

 

20,000.00 cpo

 

ሎት 4

 

አላቂ የህክምና ዕቃዎች ግዥ

 

50,000.00 cpo

 

ሎት 5

 

አላቂ የትምህርት ዕቃዎች ግዥ

 

50,000.00 cpo

 

ሎት 6

 

ሌሎች አላቂ ዕቃዎች ግዥ

 

20,000.00 cpo

 

ሎት 7

 

የተለያዩ መሳሪያና መጻህፍት ግዥ

 

10,000.00 cpo

 

ሎት 8

 

ለመስተንግዶ ግዥ

 

10,000.00 cpo

 

ሎት 9

 

ለተሸከርካሪዎችና ሌሎች ዕድሳት ግዥ

 

10,000.00 cpo

 

ሎት: 10

 

ለህንጻ ለቁሳቁስና ገጣጣምዎች ዕድላትና ጥገና

 

30.000.00 cpo

 

ሎት 11

 

በውል የሚፈፀም የሙያ አገልግሎት

20,000.00 cpo

 

ሎት 12

 

ለፕላንት፣ለማሽነር መሳሪያና ህክምና ቋሚ ዕቃዎች ግዥ

150,000 cpo

 

ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የግዥና ፋይናንስ መመሪያዎችን የምታሟሉ : ተጫራቾች  በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡

1.በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን  ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።

2. በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ መኖራቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፡፡

3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ።

4. ተጨማሪ እሴት ታክስVAT/ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።

5. በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ተጫራቾች ከተደራጁበት ክፍለ ከተማ ወይም ወረዳ በመስሪያ ቤቱ የፅህፈት ቤት ኃላፊ ስም የተፈረመ ወቅታዊ የድጋፍ ደብዳቤ እና አምራች መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።

6. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የያዘ ሰነድ ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአካውንት ቁጥር 1000640967181 በመክፈል ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 የስራ ቀናት እስከ 11ኛው ቀን 4:00 ሰዓት ድረስ ከማዕከሉ ከፋይናንስ ዳይሬክቶሬት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡

7. ተጫራቾች የሚረቱበትን ዋጋ በገዙት የጨረታ ሰነድ ላይ በስፔስፊኬሽኑ መሰረት ብቻ በማድረግ ቫትን ጨምረ ው ሞልተው በታሽገው ኤንቨሎፕ ላይ ፋይናንሻል ኦርጅናልና ኮፒ ቴክኒካል ሰነድ ኦርጅናልና ኮፒ ብለው በአራት ፖስታ በመለየት የግዥ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ከላይ በሰንጠረዥ በተገለፀው መሰረት ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።

8. ተጫራቾች ሌሎች መረጃዎችን ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

9. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

10. ጨረታው በሚከፈትበት ቀን የስራ ቀን ካልዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል።

11. ተጫራቾች ናሙና ለተጠየቀባቸው እቃዎች ናሙና ማቅረብ አለባቸው፡፡

12. የጨረታ ማስከበሪያ በcpo ነው፡፡

ማሳሰቢያ፡ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 11ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ውክልና ያላቸው አካላት በተገኙበት ጨረታው ይከፈታል።

አድራሻ ፡- እቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ጀርባ 500 ሜትር ገባ ብሎ ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶ እና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል 1ኛ ፎቅ የግዥ፣ ንብረትና ህንፃ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ

ስልክቁጥር፡-01114378666

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል


Tender details

  • Deadline: 2026-09-25
  • Bid closing time: 12:00
  • Bid closing (note): የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 11ኛው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-09-25 12:00
  • Bid opening (note): የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 11ኛው የስራ ቀን 4፡30 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Addis Ababa City Administration Lnegewa Setoch Rehabilitation Center
  • Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
  • Bid document price: ለእያንዳንዱ ሎት 200 (ሁለት መቶ ብር)
  • Published on: Addis Zemen (Sep 13, 2026)
  • Posted at: 2026-09-14T07:19:46.000Z
  • Source: 2merkato
← Back to all tenders