ኤን.ኤፍ.ኤ ቢዝነስ ኃላ.የተ.የግል ማኅበር ኦርጅናል እና አዲስ፣ የግሬደር፣ የኤክስካቫተር፣ የዶዘር፣ የሮለር፣ የባስ መለዋወጫዎችን እንዲሁም ሲገለገልባቸው የነበሩ ቀላል ተሽከርካሪዎችን እና ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

ኦርጅናል እና አዳዲስ የባስ፣ ግሬደር፣ የዶዘር የኤክስካቫተር እና የሮለር መለዋወጫዎች እንዲሁ ያገለገሉ ቀላል ተሽከርካሪዎች የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ

ድርጅታችን ኤን.ኤፍ.ኤ ቢዝነስ ኃላ.የተ.የግል ማኅበር ኦርጅናል እና አዲስ የግሬደር፣ የኤክስካቫተር፣ የዶዘር፣ የሮለር የባስ መለዋወጫዎችን እንዲሁም ሲገለገልባቸው የነበሩ ቀላል ተሽከርካሪዎችን እና ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ከሚያዚያ ጀምሮ 13፣ 14፣ 15፣ 16፣17፣19 እስከ ሚያዚያ 20 2018 ዓ.ም ድረስ ለጨረታ የተዘጋጀውን ሠነድ ከድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት እና የመለዋወጫዎቹን ሳምፕል እንዲሁም ተሽከርካሪዎቹን ማየት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን።

በጨረታ ለመሳተፍ ተጫራቾች

  • ንግድ ምዝገባ፣
  • የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣
  • የግብር ከፋይ መለያ ማስረጃ፣
  • በውክልና ከሆነ ውክልና እና መታወቂያ ይዞ መቅረብ አለበት።

ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ የተጠቀሱትን ፎቶ ኮፒ ማስረጃዎች ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው በታሸገ ኤንቨሎፕ ለዚሁ ተብሎ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

ጨረታው ሚያዚያ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ዕለት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከቀኑ በ9፡00 ሰዓት ቦሌ ቡልቡላ ማርያም ማዞሪያ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት ይከፈታል።

አሸናፊው ተጫራች በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ገንዘብን ሙሉ በመሉ በመክፈል ንብረቱን መውሰድ ይኖርበታል።

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 83 93 29 95/09 83 77 28 45

ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ለመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

 ኤን.ኤፍ.ኤ ቢዝነስ ኃላ.የተ.የግል ማኅበር


Tender details

  • Deadline: 2026-04-28
  • Bid closing time: 14:00
  • Bid opening: 2026-04-28 15:00
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: N.F.A Business P.L.C
  • Bid document price: 300.00 ብር
  • Published: Apr 19, 2026
  • Posted at: 2026-04-20T12:12:25.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders