Spare Parts and Car Decoration Materials
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ያገለገሉ የተሽከርካሪ ጎማና ባትሪዎች መሸጥ ይፈልጋል
Description
ያገለገሉ የተሸከርካሪ ጎማዎች እና ባትሪዎች
ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ያገለገሉ የተሽከርካሪ ጎማና ባትሪዎች ፍላጎት ላላቸው ተጨማሪ እሴት ታክስ (ተ.እ.ታ) ተመዝጋቢ ሆኖ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ንግድ ምዝገባ፤ ታክስ ምዝገባ ሠርቲፊኬት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና ጊዜ ያላለፈበት ታክስ ክሊራንስ ሠርተፊኬት ኮፒ ማቅረብ ለሚችሉ ድርጅቶች በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ስለሆነም ፡
1. በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልግ ድርጅት የጨረታ ሰነድ ለመግዛት በሚመጣበት ወቅት የድርጅቱን መታወቂያ ወይም ማንነታቸውን የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።
2. ተጫራቾች ዝርዝር መረጃ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ከጳጉሜ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መስከረም 12 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ በህንፃ ቁጥር 2 ምድር ቤት ላይ በሚገኘው ክፍያና ሒሳብ ማወራረጃ ሥርዓት ዳይሬክቶሬት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ስም በሂሳብ ቁጥር 7002010800001 የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) ገቢ በማድረግ እና ገቢ ያደረጉበትን ደረሰኝ ይዞ በመቅረብ በህንፃ ቁጥር 2 2ኛ ፎቅ ፋሲሊቲ ዳይሬክቶሬት በመቅረብ ለጨረታው መረጃ ማግኘትና የጨረታውን ስነድ በመግዛት መወዳደር ይችላሉ።
3. ተጫራቾች ጨረታውን ለመሳተፍ ውጤት እንደታወቀ የሚመለስ ለጎማ ብር 25,000.00 (ሃያ አምስት ሺ ብር) እና ለባትሪ ብር10,000.00 (አስር ሺ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ቢድ ቦንድ (ሲ.ፒ.ኦ) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
4. የጨረታ ሰነዱን የገዙ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከገዙበት ክፍል የበር መግቢያ ፍቃድ በመውሰድ እና የታደሰ መታወቂያ በመያዝ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ም ጎማና ባትሪዎችን ማየት ይቻላሉ።
5. ተጫራቶች ያገለገሉ የተሸከርካሪ ጎማ እና ባትሪ የሚገዙበትን ዋጋ ማስረከቢያ ቅፅ ላይ በማካተት በስም በታሸገ ኢ ነቨሎፕ ሙሉ አድራሻውን እና የጨረታውን ቁጥር በመጥቀስ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በህንፃ ቁጥር 2 ሁለተኛ ፎቅ ፋሲሊቲ ዳይሬክቶሬት መስከረም 12 ቀን 2019 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
6. ለተሸከርካሪ ጎማ እና ባትሪ ጨረታ ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሚገኘው መሰብሰቢያ አዳራሽ መስከረም 12 ቀን 2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡15 ሰዓት ይከፈታል።
7. መስሪያ ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ
በስልክ ቁጥር 011 517 5193 / 011 517 5223 ደውሎ መጠየቅ ይችላል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
Tender details
- Deadline: 2026-09-22
- Bid closing time: 10:00
- Bid opening: 2026-09-22 10:15
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: National Bank of Ethiopia
- Buyer address: Addis Ababa, Ethiopia
- Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
- Bid document price: 100 (አንድ መቶ ብር)
- Published on: Reporter (Sep 06, 2026)
- Posted at: 2026-09-07T11:41:39.000Z
- Source: 2merkato